ደራሲያን በፊደል ማውጫ
   
 
 
ሲሳይ ንጉሱ
የደራሲው ሥራዎች
1.   ግርዶሽ(ልብወለድ)
2.   የቅናት ዛር(ልብወለድ)

ስለደራሲው በጥቂቱ
አዲስ አበባ በ፲፱፶፩ ዓ.ም. የተወለዱት ሲሳይ ንጉሡ አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በባልቻ አባነፍሶ፣ የሁለተኛ ደረጃን ደግሞ በአዲስ ከተማ አጠቃላይ ተከታትለዋል፡፡ የከፍተኛ ትምህርታቸውን በአሥመራ ዩኒቨርሲቲ ከ፲፱፸፬-፲፱፸፯ ዓ.ም. ድረስ ተምረዋል።

በዩኒቨርሲቲ ሕይወት ዙሪያና በፍቅር ታሪክ ላይ በሚያተኩረው ሰመመን በሚባለው መጽፈሐፍቸው በብዙዎች ዘንድ የታወቁት ሲሳይ ንጉሡ፣ ጉዞው፣ ግርዶሽ፣ የቅናት ዛር የተባሉ ረጃጅም ልብወለዶች አሏቸው፡፡ ጉዞው የሚለውን ኖቬላ ጨምሮ ሌሎች አጫጭር ልብወለዶችን ጽፈዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ሥነ ጥበባትና መገናኛ ብዙኃን ሽልማት በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ተሸላሚም ሆነዋል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት የደራሲያን ማኀበር ዋና ጸሐፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡

ምንጭ: የኢትዮዽያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
   
   
       
 
   
     
       

መጸሐፍ ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ

ተመዝግበው ከሆነ እዘህ ይጫኑ
     
 

መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com