ደራሲያን በፊደል ማውጫ
   
 
 
ሥዩም ተፈራ
የደራሲው ሥራዎች
1.   ቤቱ(ተውኔት)
2.   ድኾቹ [ ያልታተመ ](ተውኔት)

ስለደራሲው በጥቂቱ
ሥዩም ተፈራ ጥቅምት ፲፬ ቀን ፲፱፵፫ ዓ.ም. አዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ፡፡ የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ሚኒልክ ት/ቤት አዲስ አበባ ከተማ ተከታትለዋል። ከአ.አ.ዩኒቨርሲቲም በቴአትር ሙያ ሥልጠና ወስደዋል፡፡

የሙሉ ጊዜ የመድረክ ተውኔቶችን፣ ሙዚቃዊ ድራማዎችን አዘጋጅተዋል፡፡ ከሥራዎቻቸው መካከል “ቤቱ”፣ “ሐሙስ”፣ “ዱላው”፣ የተሰኙ ቴአትሮች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በመዘጋጃ ቴአትር ቤትና በራስ ቴአትር አዘጋጅ፣ ጸሐፌ ተውኔትና ተዋናይ በመሆን አገልግለዋል፡፡ “ይፈለጋል”፣ በሚል ርዕስ በቀረበ ፊልም መሪ ተዋናይ ሆነው ሠርተዋል፡፡ “ሦስት ዕንባዎች”፣ በሚል ርዕስ የግጥም መድብል አሳትመዋል፡፡

ምንጭ: የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
   
   
       
 
   
     
       

መጸሐፍ ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ

ተመዝግበው ከሆነ እዘህ ይጫኑ
     
 

መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com