ፍቅረድንግል በየነ በአዲስ አበባ ከተማ በ፲፱፴፪ ዓ.ም. ተወለዱ። የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቅድስት ሥላሴ ት/ቤት አጠናቀቁ፡፡ ከዚያም የከፍተኛ ትምህርታቸውን በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በሥነ ጽሑፍና ቋንቋ አማርኛና እንግሊዝኛ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ሲሆን በዚሁ ዩኒቨርሲቲ በድኀረ ምረቃ ፕሮግራም የማስተርስ ዲግሪያቸውን ወስደዋል፡፡
ፍቅረድንግል በየነ “ዕሌኒ ንግሥት” ቴአትር “12ኛው ሌሊት” ትርጉም ከሼክስፒር “የምሳሌያዊ ንግግሮች ሰዋስው ትንታኔ” “የሳይንስ ራዕይ” “ልቦለድ መጽሐፍ” ለአንባቢያን አቅበዋል፡፡ የሬዲዮ ድራማዎችንም ጽፈው ለአድማጮች አድርሰዋል፡፡
ምንጭ: የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ። |