ደራሲያን በፊደል ማውጫ
   
 
 
ወንድሙ ነጋሽ ደስታ
የደራሲው ሥራዎች
1.   ፍጻሜው ሲያምር( ትርጉም)

ስለደራሲው በጥቂቱ
ወንድሙ ነጋሽ ደስታ መስከረም ፲፮ ቀን ፲፱፴፰ ዓ.ም. በጅማ ከተማ ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሞጆ ሚያዝያ 27 ት/ቤት ጅማ፣ የሁለተኛ ደረጃን በኮከበ ጽባሕ አዲስ አበባ ተከታትለዋል፡፡ ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ-ጽሑፍ ክፍል፣ በሥነ- ጽሑፍ ተመርቀዋል፡፡

ወንድሙ ነጋሽ ደስታ “ከሼክስፒር ሥራዎች” “ፍጻሜው ሲያምር”፣ እና “ወዳጅ ሲከዳ”፣ በመባል የሚታወቁትን የሼክስፒር ሥራዎችን ተርጉመው አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም “እንቡጥ ጽጌረዳ” በተሰኘው ረዥም ልቦለድ ሥራቸው ይታወቃሉ፡፡

ምንጭ: የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
   
   
       
 
   
     
       

መጸሐፍ ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ

ተመዝግበው ከሆነ እዘህ ይጫኑ
     
 

መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com