ታከለ ወልደሀዋርያትን ከአብዛኛው ሰው የሚለየው ጠባይ ቢኖር ዛሬ ስለተሸነፈ ትግሉን ያለማቋረጡ ነው። ልጅ እያሱን ለኢትዮጵያ አይበጅም ብሎ ባመነበት ሰአት ልጅእያሱን ለማስወገድ በሙሉ ልቦናውና በሙሉ አቅሙ ታገለ።
...አሁን ደግሞ ተፈሪ ማለፍአለበት ነገር ግን ተፈሪን እጥላለሁ ማለት ኢትዮጵያን እስካልጎዳ ድረስ ብቻ ነው። ምክንያቱም ተፈሪ ያልፋል፣ታከለም ያልፋል፣ የምትዘልቀው ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ስለዚህም የታከለ አላማ እስከ ህይወቱ መጨረሻ ድረስ የሚከተለው ይሆናል። |