የኢትዮዽያ ደራሲያን በፊደል ማውጫ
 
     
9 ውጤት ተገኝቷል
   
 
በቀለ ተገኝ የምእራባውያን ሥልጣኔ መሰረት ያደረገውን ፍልስፍና እንዲሁም ተያይዞ የመጣውን ስልጣኔ በስፋት የሚዳስስ ግሩም የሆነ መጸሐፍ ነው።
የምእራባውያን ሥልጣኔ መሰረት ያደረገውን ፍልስፍና እንዲሁም ተያይዞ የመጣውን ስልጣኔ በስፋት የሚዳስስ ግሩም የሆነ መጸሐፍ ነው።
 
እጓለ ገብረ ዮሐንስ ከመጽሐፉ የተወሰደ
“ሰው ሀብታም ሆነ ደሀ ልዩነቱ የሚታየው በዝቅተኛ የዕውቀት እና የእምነት ደረጃ እስካለ ድረስ ብቻ ነው። ወደ ላይ ከፍ ካሉ በኋላ ወደ ፍጹምነት ደረጃ ሲደርሱማ የሚያስቡለት የሚሰስቱለት ነገር አይሆንም። እዚህ ከፍታ ላይ ያለ ሰው ብዙ ቢኖረው አይተርፈውም። ስለሚያካፍል፤ ትንሽም ያለው አያንሰውም። ብዙ ስለማይፈልግ ነው። ወደዚህ ዓለም ይዞት የመጣው፣ ሲሔድም የሚያከትለው አንዳች ነገር አለመኖሩን ያውቃልና ነው”
ሀገር፣መንደር፣ቤት ንብረቱን ትቶ ወደ ሩቅ የሄደ ሰው ባይተዋር ይባላል። ይህ ስያሜ በኑሮ አድራሻ መለወጥ ብቻ ምክንያቱን የሚያገኝ አይደለም ።የመንፈስ ባይተዋርነትም አለ። ሰው ከነበረበት ቦታ ወደ ሌላ ሳይዘዋወርም ለአዲስ አስተሳተሰብ፣ ፈሊጥና የኑሮ መልክ ሊጋለጥ ይችላል።አንደኛው እስኪያይል ወይም ሁለቱም እስኪዋሐዱ ድረስ የወትሮው እና የአሁኑ በህሊና ውስጥ የባላንጣዎች ተቃርኖ ይፈጥራሉ። እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው የቸልተኝነት የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል። " አስመሳይ፤ አድር ባይ እንደ እምነቱ የማይኖር እንደ ኑሮው የማያምን የሕሊናውን ብኩርና ለምስር ንፍሮ የለወጠ" ሌላም ሌላም እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል። "የሞራል ድቀት" የሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራልን? የመነሳቱ፣ የመቆሙ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠብቆ የመራመዱ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።

~ የተመረጡ ስለመጽሐፉ የተጻፉ ግምገማዎች:

1. “ስለ ክርስቲያን ሥነ-ምግባር መሠረት” ብፁዓን ንጹሓነ ልብ፤ ገጽ 165“

ያ ሰው ሞተ አሉኝ፣ እንዴት ያ ሰው ይሙት?
በሕይወት ሲያስተምር፣ ለሰው ልጆች ሕይወት፣
ተቀበረ አሉኝ፣ ከቶ እንዴት ይቀበር፣
ሙት ሕያው እንዲሆን፣ በቁሙ ሲያስተምር!

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
ከመጽሐፉ የተወሰደ
“ሰው ሀብታም ሆነ ደሀ ልዩነቱ የሚታየው በዝቅተኛ የዕውቀት እና የእምነት ደረጃ እስካለ ድረስ ብቻ ነው። ወደ ላይ ከፍ ካሉ በኋላ ወደ ፍጹምነት ደረጃ ሲደርሱማ የሚያስቡለት የሚሰስቱለት ነገር አይሆንም። እዚህ ከፍታ ላይ ያለ ሰው ብዙ ቢኖረው አይተርፈውም። ስለሚያካፍል፤ ትንሽም ያለው አያንሰውም። ብዙ ስለማይፈልግ ነው። ወደዚህ ዓለም ይዞት የመጣው፣ ሲሔድም የሚያከትለው አንዳች ነገር አለመኖሩን ያውቃልና ነው”
ሀገር፣መንደር፣ቤት ንብረቱን ትቶ ወደ ሩቅ የሄደ ሰው ባይተዋር ይባላል። ይህ ስያሜ በኑሮ አድራሻ መለወጥ ብቻ ምክንያቱን የሚያገኝ አይደለም ።የመንፈስ ባይተዋርነትም አለ። ሰው ከነበረበት ቦታ ወደ ሌላ ሳይዘዋወርም ለአዲስ አስተሳተሰብ፣ ፈሊጥና የኑሮ መልክ ሊጋለጥ ይችላል።አንደኛው እስኪያይል ወይም ሁለቱም እስኪዋሐዱ ድረስ የወትሮው እና የአሁኑ በህሊና ውስጥ የባላንጣዎች ተቃርኖ ይፈጥራሉ። እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው የቸልተኝነት የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል። " አስመሳይ፤ አድር ባይ እንደ እምነቱ የማይኖር እንደ ኑሮው የማያምን የሕሊናውን ብኩርና ለምስር ንፍሮ የለወጠ" ሌላም ሌላም እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል። "የሞራል ድቀት" የሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራልን? የመነሳቱ፣ የመቆሙ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠብቆ የመራመዱ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።

~ የተመረጡ ስለመጽሐፉ የተጻፉ ግምገማዎች:

1. “ስለ ክርስቲያን ሥነ-ምግባር መሠረት” ብፁዓን ንጹሓነ ልብ፤ ገጽ 165“

ያ ሰው ሞተ አሉኝ፣ እንዴት ያ ሰው ይሙት?
በሕይወት ሲያስተምር፣ ለሰው ልጆች ሕይወት፣
ተቀበረ አሉኝ፣ ከቶ እንዴት ይቀበር፣
ሙት ሕያው እንዲሆን፣ በቁሙ ሲያስተምር!

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
 
 
 

 
 
 
 
   
       

መጸሐፍ ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ

ተመዝግበው ከሆነ እዘህ ይጫኑ
 

መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com