የኢትዮዽያ ደራሲያን በፊደል ማውጫ
 
     
252 ውጤት ተገኝቷል
   
 
ተክለሐዋርያት ተክለማርያም የአፄ ኀይለሥላሴን ዘመን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው እንደመስታዎት አጉልቶ የሚያሳይ ድንቅ መጽሐፍ።
የአፄ ኀይለሥላሴን ዘመን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው እንደመስታዎት አጉልቶ የሚያሳይ ድንቅ መጽሐፍ።
 
አባ ባሕርይ የኦሮሞን ታሪክ የያዘ የታሪክ መዘክር።
የኦሮሞን ታሪክ የያዘ የታሪክ መዘክር።
 
ተክለጻድቅ መኩሪያ ስለታላቁ ንጉስ አፄ ቴዎድሮስ ለኢትዮጵያ የነበራቸውን ታላቅ ራይ ለአንድነት ያደረጉትን ታላላቅ ክንውኖችና አስተዋፅዎችን የከተበ ትልቅ የታሪክ መጸሐፍ።
ስለታላቁ ንጉስ አፄ ቴዎድሮስ ለኢትዮጵያ የነበራቸውን ታላቅ ራይ ለአንድነት ያደረጉትን ታላላቅ ክንውኖችና አስተዋፅዎችን የከተበ ትልቅ የታሪክ መጸሐፍ።
 
ተክለጻድቅ መኩሪያ ስለታላቁ ንጉስ አፄ ምኒልክ ለኢትዮጵያ አንድነት ክብርና ብልፅግና ስልጣኔ እምነት ያደረጉትን ታቅ ክንውኖችና አስተዋፅዎችን የከተበ ትልቅ የታሪክ መጸሐፍ።
ስለታላቁ ንጉስ አፄ ምኒልክ ለኢትዮጵያ አንድነት ክብርና ብልፅግና ስልጣኔ እምነት ያደረጉትን ታቅ ክንውኖችና አስተዋፅዎችን የከተበ ትልቅ የታሪክ መጸሐፍ።
 
ጳውሎስ ኞኞ ስለታላቁ ንጉስ አፄ ቴዎድሮስ ለኢትዮዽያ የነበራቸውን ታላቅ ራዕይ ለኢትዮጵያ አንድነት ያደረጉትን ታላላቅ ተጋድሎና አርአያነት የከተበ የታሪክ መጸሐፍ።
ስለታላቁ ንጉስ አፄ ቴዎድሮስ ለኢትዮዽያ የነበራቸውን ታላቅ ራዕይ ለኢትዮጵያ አንድነት ያደረጉትን ታላላቅ ተጋድሎና አርአያነት የከተበ የታሪክ መጸሐፍ።

 
ባሕሩ ዘውዴ የመቶ አመት የኢትዮጵያን ታሪክ በስፋት የዳሰሰ ድንቅ የታሪክ መጸሐፍ።
የመቶ አመት የኢትዮጵያን ታሪክ በስፋት የዳሰሰ ድንቅ የታሪክ መጸሐፍ።
 
ገብረሕይወት ባይከዳኝ የዐፄ ምኒሊክ ዘመን በወጣቱ አስኳላ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ አስመራ ፩፱፲፩፪።
የዐፄ ምኒሊክ ዘመን በወጣቱ አስኳላ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ አስመራ ፩፱፲፩፪።
 
መንግስቱ ለማ መጽሐፈ ትዝታ ዘ አለቃ ለማ፤ ከአፄ ዮሃንስ ግዜ ጀምሮ የነበረውን የኢትዮጵያ የቤተክርስትያን ሊቃውንት ታሪክ በሊቁ አለቃ ለማ አንደበት ይተርካል። መቸም ቢሆን የኢትዮጵያን ሊቃውንት ታሪክ ማንበብ ያስደስታል። ነገርግን እንደዚህ በግሩም ሁኔታ የነበራቸውን የእውቀት ርቀት፣ ለእውቀት የሚሰጡት ክብርና ሞገስ፣ የእርስ በርስ አክብሮት ማርማር በሚል በሊቁ አለቃ ለማ አንደበት ሲተረክ ከማንበብ በላይ ለአንድ ኢትዮጵያዊ ምን የላቀ ንባብ ቢያገኝ ሊያስደስተው የሚችል ነገር እነዳለ አላውቅም። የነአቡነ አሮን የፃድቃን ህይወት። የነ አፄ ዮሃንስ ሀይማኖታዊ ቀናይነት። የዐፄ ቴዎድሮስ የዜማ ፍቅር። ብቻ የኢትዮጵያን ታላቅነት ሁሉም ይረዳል ነገር ግን የታላቅነትዋን ሚስጥር መሰረት የሆኑትን ሊቃውንት ታሪክ ብዙዎቻችን አናውቅም፤ እኛ የምናውቀው የነገስታቱን ታሪክ ብቻ ነው፣ ከነገስታቱ ጀርባ እነዚህ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ፋኖስ ሆነው ኢትዮዽያን ይመሯት ነበር።
መጽሐፈ ትዝታ ዘ አለቃ ለማ፤ ከአፄ ዮሃንስ ግዜ ጀምሮ የነበረውን የኢትዮጵያ የቤተክርስትያን ሊቃውንት ታሪክ በሊቁ አለቃ ለማ አንደበት ይተርካል። መቸም ቢሆን የኢትዮጵያን ሊቃውንት ታሪክ ማንበብ ያስደስታል። ነገርግን እንደዚህ በግሩም ሁኔታ የነበራቸውን የእውቀት ርቀት፣ ለእውቀት የሚሰጡት ክብርና ሞገስ፣ የእርስ በርስ አክብሮት ማርማር በሚል በሊቁ አለቃ ለማ አንደበት ሲተረክ ከማንበብ በላይ ለአንድ ኢትዮጵያዊ ምን የላቀ ንባብ ቢያገኝ ሊያስደስተው የሚችል ነገር እነዳለ አላውቅም። የነአቡነ አሮን የፃድቃን ህይወት። የነ አፄ ዮሃንስ ሀይማኖታዊ ቀናይነት። የዐፄ ቴዎድሮስ የዜማ ፍቅር። ብቻ የኢትዮጵያን ታላቅነት ሁሉም ይረዳል ነገር ግን የታላቅነትዋን ሚስጥር መሰረት የሆኑትን ሊቃውንት ታሪክ ብዙዎቻችን አናውቅም፤ እኛ የምናውቀው የነገስታቱን ታሪክ ብቻ ነው፣ ከነገስታቱ ጀርባ እነዚህ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ፋኖስ ሆነው ኢትዮዽያን ይመሯት ነበር።
 
 

 
 
 
 
 
አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ Afework Gebreyesus ደራሲ.አፈወርቅ ገብረየሲስ የምኒሊክ አማካሪ ሆነው በቅርበት ኢያውቁት ን የዘመኑን የህዝብ አስተዳደር እንዴት እንደነበር በተለይም ቀድመው ንጉስ ዩነበሪትን አጤ ዮሐንስ ዘመን ዩታዪ የህዝብ አስተዳደር ችግር እንደማመጣ ጠሮያ በመጠቀም ለምኒሊክ ቸስተደሰፈር ን በማሞካሸት የጣፉት ነው። መትሀፉ ብዙ ቁም ነገሮችን የያዘ ቢሆንም ስለአጤ ዮሐንስ የሚያቀርበውን የማነጣጠሮያ ሀተታ በጎዜው በነበሩ ምሁራን ትችትን ቸስነሰቨቷአል።
ደራሲ.አፈወርቅ ገብረየሲስ የምኒሊክ አማካሪ ሆነው በቅርበት ኢያውቁት ን የዘመኑን የህዝብ አስተዳደር እንዴት እንደነበር በተለይም ቀድመው ንጉስ ዩነበሪትን አጤ ዮሐንስ ዘመን ዩታዪ የህዝብ አስተዳደር ችግር እንደማመጣ ጠሮያ በመጠቀም ለምኒሊክ ቸስተደሰፈር ን በማሞካሸት የጣፉት ነው። መትሀፉ ብዙ ቁም ነገሮችን የያዘ ቢሆንም ስለአጤ ዮሐንስ የሚያቀርበውን የማነጣጠሮያ ሀተታ በጎዜው በነበሩ ምሁራን ትችትን ቸስነሰቨቷአል።

 
 
 
 
 

 
 
ማህተመሥላሴ ወልደመስቀል ከ1900 እስከ 1935 ዓ.ም የነበረውን የኢትዮጵያ አስተዳደር ስርአት ወግና ደንብ በሚገባ የሚያብራራ መጽሐፍ።
ከ1900 እስከ 1935 ዓ.ም የነበረውን የኢትዮጵያ አስተዳደር ስርአት ወግና ደንብ በሚገባ የሚያብራራ መጽሐፍ።
 
 
 

 
 
 
 
 

 
 
 
 
 

 
 
 
 
ታምራት አማኑኤል

ጽሑፉ ፡ የፕሮፌሰር ፡ ታምራት ፡ አማኑኤል ፡ ነው። ፕሮፌሰር ፡ ታምራት ፡ ከዛሬ ፡ ኻያዐምስት ፡ ዓመታት ፡ በፊት ፡ በትምርትና ፡ ሥነጥበብ ፡ ሚኒስቴር ፡ አማካሪ ፡ ኾነው ይሠሩ ፡ ነበር።ነገር ፡ ግን ፡ በዚያን ፡ ጊዜ ፡ ፕሮፌሰር ፡ በመባል ፡ ፈንታ ፡ ሊቀማእምራን ፡ ይባሉ ፡ ነበር።

ትዝ ፡ እንደሚለኝ ፡ ባ፲፱፻፴፮ ፡ ዓ.ም ፡ በቱርክ ፡ አ ገር ፡ የሚገኝ ፡ አካዳሚ ፡ ይኹን ፡ ወይም ፡ የደራሲያን ፡ ማኅበር ፡ ስለኢትዮጵያ ፡ ሥነጽሑፍና ፡ ስለኢትዮጵያዊያን ፡ ደራሲያን ፡ ጠይቆ ፡ ስለነበረ ፡ ጥያቄውን ፡ የመለሱት ፡ ሊቀ ማእምራን ፡ ታምራት ፡ አማኑኤል ፡ ነበሩ።

በዚህ ፡ ምክንያት ፡ ስለኢትዮጵያ ፡ ሥነጽሑፍና ፡ ስለኢትዮጵያዊያን ፡ ደራሲያን ፡ ከብዙ ፡ በጥቂቱ ፡ የምታመ ለክተውን ፡ ይህችን ፡ ጽሑፍ ፡ ሊቀማእምራኑ ፡ በዐማርኛ ፡ አዘጋጅተው ፡ አቀረቡ።ነገር ፡ ግን ፡ ጠያቂው ፡ የውጪአገር ፡ ድርጅት ፡ በመኾኑ ፡ መጠን ፡ መግለጫውም ፡ በውጭ ፡ ቋንቋ ፡ መዘጋጀት ፡ ነበረበት። ስለዚህ ፡ ጽሑፊቱ በእንግሊዝኛ ፡ እንድትተረጐም ፡ በዚያን ፡ ዘመን ፡ እኔ ፡ ጽሑፎችን ፡ በማረም ፡ ሥራ ፡ አገለግልበት ፡ ወደነበረው ፡ ክፍል ፡ ተላከች።የፕሮፌሰሩ ፡ ዐማርኛ ፡ ጽሑፍም ፡ በዚያን ጊዜ ፡ እንግሊዝኛ ፡ ተርጓሚ ፡ ለነበሩት ፡ ለአቶ ፡ እንግዳ ፡ ጽጌሐና ፡ ጥቂት ፡ ከባድ ፡ ኾኖ ፡ የዐማርኛውን ፡ አስተሳሰብ በእንግሊዝኛ ፡ አስተካክለው ፡ ለመግለጥ ፡ አስቸጋሪ ፡ ስለ ኾነባቸው ፡ በማስረዳቱ ፡ ሥራ ፡ እንድረዳቸው ፡ ታዝዤ ፡ ዐብረን ፡ ከሠራን ፡ በኋላ ፡ እንግሊዝኛው ፡ ሲላክ ፡ ይህ ፡ ዐማርኛው ፡ ግን ፡ እኛው ፡ ዘንድ ፡ ቀረ።

የጽሑፉ ፡ አሰካክና ፡ አገላለጥ፣የታሪኩም ፡ አቀራ ረብና ፡ ውበት ፡ ደስ ፡ ስለሚለኝ ፡ ጽሑፉን ፡ ዐልፎ ፡ ዐልፎ እመለከተው ፡ ነበር። ነፍሳቸውን ፡ ይማርና ፡ በሕይወት ፡ ቢኖሩ ፡ ኖሮ ፡ ከዚህም ፡ የተሻለ ፡ ጽሑፍ ፡ ለአገራቸው ፡ ሕዝብ ፡ እንዲያበረክቱ ፡ ማሳሰብ ፡ ይቻል ፡ ነበር ፡ ይኾናል። ባለመኖራቸው ፡ አልተቻለም። ካኹን ፡ ቀድሞም ፡ ‘ማህአ ትማ ፡ ጋንዲ’ ፡ ከሚባለው ፡ በቀር ፡ በስማቸው ፡ ታትሞ ፡ የወጣ ፡ ሌላ ፡ ጽሑፍ ፡ መኖሩን ፡ አላውቅም።

ይህችም ፡ ጽሑፍ ፡ በመጽሐፍነት ፡ ለመውጣት የሚያበቃት ፡ መጠን ፡ ባይኖራትም ፡ በኾነው ፡ መንገድ ፡ ቁምነገር ፡ ላይ ፡ ብትውል ፡ ያንኑ ፡ ያኽል ፡ ለስማቸው ፡ መጠሪያ ፡ ልትኾን ፡ ትችል ፡ ነበር ፡ እያልኹ ፡ በማሰላስል በት ፡ ጊዜ ፡ በቀዳማዊ ፡ ኀይለሥላሴ ፡ ዩኒቨርስቲ ፡ ለሚገኘ ው ፡ ለኢትዮጵያ ፡ ቋንቋዎችና ፡ ሥነጽሑፍ ፡ ክፍል ፡ ብት ቀርብ ፡ ለምርምርና ፡ ለጥናት ፡ ትረዳለች፣በመጽሔትም ታትማ ፡ ትወጣና ፡ ለፕሮፌሰሩ ፡ ዝክረ ፡ ስም ፡ ትኾናለች በሚል ፡ አስተሳሰብ ፡ ከሥራ ፡ ጓደኛዬ ፡ ካቶ ፡ አሰፋ ፡ ገብረ ማሪያም ፡ ጋር ፡ ከተመካከርንበት ፡ በኋላ ፡ በዚሁ ፡ ተግባር ላይ ፡ እንድትውልላቸው ፡ የኒህን ፡ ታላቅ ፡ ምሁር ፡ ስምና ሥራ ፡ የምታስታውስውን ፡ ይህችን ፡ በ፳፩ ፡ ገጽ ፡ የተጻፈች ትንሽ ፡ ጽሑፍ ፡ ለዚሁ ፡ ድርጅት ፡ አቀረብኋት።

ከበደ ፡ ደስታ ፲፱፻፷፩ ዓ.ም

ስለኢትዮጵያ ፡ ደራሲያን። ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ጽሑፉ ፡ የፕሮፌሰር ፡ ታምራት ፡ አማኑኤል ፡ ነው። ፕሮፌሰር ፡ ታምራት ፡ ከዛሬ ፡ ኻያዐምስት ፡ ዓመታት ፡ በፊት ፡ በትምርትና ፡ ሥነጥበብ ፡ ሚኒስቴር ፡ አማካሪ ፡ ኾነው ይሠሩ ፡ ነበር።ነገር ፡ ግን ፡ በዚያን ፡ ጊዜ ፡ ፕሮፌሰር ፡ በመባል ፡ ፈንታ ፡ ሊቀማእምራን ፡ ይባሉ ፡ ነበር።

ትዝ ፡ እንደሚለኝ ፡ ባ፲፱፻፴፮ ፡ ዓ.ም ፡ በቱርክ ፡ አ ገር ፡ የሚገኝ ፡ አካዳሚ ፡ ይኹን ፡ ወይም ፡ የደራሲያን ፡ ማኅበር ፡ ስለኢትዮጵያ ፡ ሥነጽሑፍና ፡ ስለኢትዮጵያዊያን ፡ ደራሲያን ፡ ጠይቆ ፡ ስለነበረ ፡ ጥያቄውን ፡ የመለሱት ፡ ሊቀ ማእምራን ፡ ታምራት ፡ አማኑኤል ፡ ነበሩ።

በዚህ ፡ ምክንያት ፡ ስለኢትዮጵያ ፡ ሥነጽሑፍና ፡ ስለኢትዮጵያዊያን ፡ ደራሲያን ፡ ከብዙ ፡ በጥቂቱ ፡ የምታመ ለክተውን ፡ ይህችን ፡ ጽሑፍ ፡ ሊቀማእምራኑ ፡ በዐማርኛ ፡ አዘጋጅተው ፡ አቀረቡ።ነገር ፡ ግን ፡ ጠያቂው ፡ የውጪአገር ፡ ድርጅት ፡ በመኾኑ ፡ መጠን ፡ መግለጫውም ፡ በውጭ ፡ ቋንቋ ፡ መዘጋጀት ፡ ነበረበት። ስለዚህ ፡ ጽሑፊቱ በእንግሊዝኛ ፡ እንድትተረጐም ፡ በዚያን ፡ ዘመን ፡ እኔ ፡ ጽሑፎችን ፡ በማረም ፡ ሥራ ፡ አገለግልበት ፡ ወደነበረው ፡ ክፍል ፡ ተላከች።የፕሮፌሰሩ ፡ ዐማርኛ ፡ ጽሑፍም ፡ በዚያን ጊዜ ፡ እንግሊዝኛ ፡ ተርጓሚ ፡ ለነበሩት ፡ ለአቶ ፡ እንግዳ ፡ ጽጌሐና ፡ ጥቂት ፡ ከባድ ፡ ኾኖ ፡ የዐማርኛውን ፡ አስተሳሰብ በእንግሊዝኛ ፡ አስተካክለው ፡ ለመግለጥ ፡ አስቸጋሪ ፡ ስለ ኾነባቸው ፡ በማስረዳቱ ፡ ሥራ ፡ እንድረዳቸው ፡ ታዝዤ ፡ ዐብረን ፡ ከሠራን ፡ በኋላ ፡ እንግሊዝኛው ፡ ሲላክ ፡ ይህ ፡ ዐማርኛው ፡ ግን ፡ እኛው ፡ ዘንድ ፡ ቀረ።

የጽሑፉ ፡ አሰካክና ፡ አገላለጥ፣የታሪኩም ፡ አቀራ ረብና ፡ ውበት ፡ ደስ ፡ ስለሚለኝ ፡ ጽሑፉን ፡ ዐልፎ ፡ ዐልፎ እመለከተው ፡ ነበር። ነፍሳቸውን ፡ ይማርና ፡ በሕይወት ፡ ቢኖሩ ፡ ኖሮ ፡ ከዚህም ፡ የተሻለ ፡ ጽሑፍ ፡ ለአገራቸው ፡ ሕዝብ ፡ እንዲያበረክቱ ፡ ማሳሰብ ፡ ይቻል ፡ ነበር ፡ ይኾናል። ባለመኖራቸው ፡ አልተቻለም። ካኹን ፡ ቀድሞም ፡ ‘ማህአ ትማ ፡ ጋንዲ’ ፡ ከሚባለው ፡ በቀር ፡ በስማቸው ፡ ታትሞ ፡ የወጣ ፡ ሌላ ፡ ጽሑፍ ፡ መኖሩን ፡ አላውቅም።

ይህችም ፡ ጽሑፍ ፡ በመጽሐፍነት ፡ ለመውጣት የሚያበቃት ፡ መጠን ፡ ባይኖራትም ፡ በኾነው ፡ መንገድ ፡ ቁምነገር ፡ ላይ ፡ ብትውል ፡ ያንኑ ፡ ያኽል ፡ ለስማቸው ፡ መጠሪያ ፡ ልትኾን ፡ ትችል ፡ ነበር ፡ እያልኹ ፡ በማሰላስል በት ፡ ጊዜ ፡ በቀዳማዊ ፡ ኀይለሥላሴ ፡ ዩኒቨርስቲ ፡ ለሚገኘ ው ፡ ለኢትዮጵያ ፡ ቋንቋዎችና ፡ ሥነጽሑፍ ፡ ክፍል ፡ ብት ቀርብ ፡ ለምርምርና ፡ ለጥናት ፡ ትረዳለች፣በመጽሔትም ታትማ ፡ ትወጣና ፡ ለፕሮፌሰሩ ፡ ዝክረ ፡ ስም ፡ ትኾናለች በሚል ፡ አስተሳሰብ ፡ ከሥራ ፡ ጓደኛዬ ፡ ካቶ ፡ አሰፋ ፡ ገብረ ማሪያም ፡ ጋር ፡ ከተመካከርንበት ፡ በኋላ ፡ በዚሁ ፡ ተግባር ላይ ፡ እንድትውልላቸው ፡ የኒህን ፡ ታላቅ ፡ ምሁር ፡ ስምና ሥራ ፡ የምታስታውስውን ፡ ይህችን ፡ በ፳፩ ፡ ገጽ ፡ የተጻፈች ትንሽ ፡ ጽሑፍ ፡ ለዚሁ ፡ ድርጅት ፡ አቀረብኋት።

ከበደ ፡ ደስታ ፲፱፻፷፩ ዓ.ም

ስለኢትዮጵያ ፡ ደራሲያን። ሙሉ ጽሑፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
 
ከበደ ተሰማ የዚህ : የታሪክ : ማስታወሻ : ረቂቅ : የጻፍሁት : በ፲፱፻፴ : ዓ.ም : ኢየሩሳሌም : ላይ : በስደት : ሳለሁ : ነበር፤ የኢትዮጵያ : የነጻነት :ጮራ : በፈነጠቀበት : ጊዜ : ቀዳሚ : መልክተኛ : ሆኜ : በሱዳን : በኩል : ወደ : ኢትዮጵያ : በገባሁ : ጊዜ : ረቂቁ : ከጓዝ : ጋር : ቋራ : ላይ : ቀርቶ : ነበርና : ጠፋብኝ። ቢሆንም፤ ታሪኩ : በአእምሮዬ : ውስጥ : ተቀርጾ : ሁል : ጊዜ : ትዝ : ይለን : ስለነበር : በ፲፱፻፴፱:ዓ.ም : የዚህን : ማስታወሻ : ረቂቅ : በድጋሚ : ጻፍኩት።
የዚህ : የታሪክ : ማስታወሻ : ረቂቅ : የጻፍሁት : በ፲፱፻፴ : ዓ.ም : ኢየሩሳሌም : ላይ : በስደት : ሳለሁ : ነበር፤ የኢትዮጵያ : የነጻነት :ጮራ : በፈነጠቀበት : ጊዜ : ቀዳሚ : መልክተኛ : ሆኜ : በሱዳን : በኩል : ወደ : ኢትዮጵያ : በገባሁ : ጊዜ : ረቂቁ : ከጓዝ : ጋር : ቋራ : ላይ : ቀርቶ : ነበርና : ጠፋብኝ። ቢሆንም፤ ታሪኩ : በአእምሮዬ : ውስጥ : ተቀርጾ : ሁል : ጊዜ : ትዝ : ይለን : ስለነበር : በ፲፱፻፴፱:ዓ.ም : የዚህን : ማስታወሻ : ረቂቅ : በድጋሚ : ጻፍኩት።

 
መርስዔ ሐዘን ወልደ ቂርቆስ መርሰዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፤ አንድ ለእናቱ ለኢትዮጵያ አንተ ቀጥቀጥትከ አርእስቲሁ ለዕበድ፤ወወሀብኮሙ ለዋስዎሙ ለዘሕዝበ ኢትዮጵያ ውሉድ።
ክቡር ብላታ መርስዔ ሐዘን ወልደ ቂርቆስ ለኢትዮጵያ የሰጡትን ልባዊ አገልግሎትና እሳቸውንም በአካል የሚያውቅ ሰው በየምእት ዓመት አንድ ጊዜ የሚታዩ የዕውቀትና የጥበብ ሰዎች ካሉ ክቡርነታቸው አንዱ መሆናቸውን አይጠራጠርም።...
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ

... መጽሐፉ በ1896 ዓ.ም. እስከ 1922 ዓ.ም ያለውን ዘመን የታሪክ መረጃዎች የመዘገበ በቋሚ ምስክርነት የቀረበ በመሆኑ ለቄየው ፣ ላሁኑና ለመጪው ትውልድ ግንዛቤና ትምህርት እንደሚሰጥ አምናለሁ።...
-ደጃዝማች ዘውዴ ገብረ ሥላሴ

...እነሆ ባንድ ቅፅ ተጠቃለው ለኅትመት የበቁት የብላታ መርስዔ ኀዘን ትዝታዎች የሀገራችንን የሐያኛው መቶ ዓመት መጀመሪያ ዐሠርት ዓመታት በዝርዝር ለማወቅ ለሚሻ አንባቢ ትልቅ የታሪክ ድግስ ይዘው ቀርበዋል። ለታሪክ ተማሪዎችና ለተመራማሪዎችም ካጠገባቸው ሊለይ የማይችል የሰነድ ስንቅ ነው።...
- ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ
መርሰዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፤ አንድ ለእናቱ ለኢትዮጵያ አንተ ቀጥቀጥትከ አርእስቲሁ ለዕበድ፤ወወሀብኮሙ ለዋስዎሙ ለዘሕዝበ ኢትዮጵያ ውሉድ።
ክቡር ብላታ መርስዔ ሐዘን ወልደ ቂርቆስ ለኢትዮጵያ የሰጡትን ልባዊ አገልግሎትና እሳቸውንም በአካል የሚያውቅ ሰው በየምእት ዓመት አንድ ጊዜ የሚታዩ የዕውቀትና የጥበብ ሰዎች ካሉ ክቡርነታቸው አንዱ መሆናቸውን አይጠራጠርም።...
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ

... መጽሐፉ በ1896 ዓ.ም. እስከ 1922 ዓ.ም ያለውን ዘመን የታሪክ መረጃዎች የመዘገበ በቋሚ ምስክርነት የቀረበ በመሆኑ ለቄየው ፣ ላሁኑና ለመጪው ትውልድ ግንዛቤና ትምህርት እንደሚሰጥ አምናለሁ።...
-ደጃዝማች ዘውዴ ገብረ ሥላሴ

...እነሆ ባንድ ቅፅ ተጠቃለው ለኅትመት የበቁት የብላታ መርስዔ ኀዘን ትዝታዎች የሀገራችንን የሐያኛው መቶ ዓመት መጀመሪያ ዐሠርት ዓመታት በዝርዝር ለማወቅ ለሚሻ አንባቢ ትልቅ የታሪክ ድግስ ይዘው ቀርበዋል። ለታሪክ ተማሪዎችና ለተመራማሪዎችም ካጠገባቸው ሊለይ የማይችል የሰነድ ስንቅ ነው።...
- ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ
 
 
 
 

 
 
 
 
 
ማሞ ውድነህ ለዶጋሊ ድል መቶኛ አመት መታሰቢያ ። በደራሲ ማሞ ውድነህ የተዘጋጀ።
ለዶጋሊ ድል መቶኛ አመት መታሰቢያ ። በደራሲ ማሞ ውድነህ የተዘጋጀ።

 
 
 
በላይ ግደይ በትግሪኛ የተጻፈ
በትግሪኛ የተጻፈ
 
 

 
 
 
 
 

 
 
 
 
 
ዘነበ ፈለቀ የደርግ ዘመንን የፖለቲካ ሂደት የሚዳስስ መጽሐፍ።
የደርግ ዘመንን የፖለቲካ ሂደት የሚዳስስ መጽሐፍ።

 
 
 
 
 

 
 
 
 
 

 
ብርሃኑ ለሜሳ ከታቦር ታሚ ጋር በመሆን የጻፉት።
ከታቦር ታሚ ጋር በመሆን የጻፉት።
 
 
 
 

 
 
 
 
 

 
 
ኦቶ ባዮግራፊ
 
ኦቶ ባዮግራፊ
 
 

 
 
ፍጹም ወልደማርያም ለአዲሱ ትውልድ ነባርና ታላላቅ ደራሲያንን እያስተዋወቀ ወደታላላቅስራዎቻቸውን የበለጠ ለማወቅ የሚያጓጓ መጽሐፍ ነው።
ለአዲሱ ትውልድ ነባርና ታላላቅ ደራሲያንን እያስተዋወቀ ወደታላላቅስራዎቻቸውን የበለጠ ለማወቅ የሚያጓጓ መጽሐፍ ነው።
 
ብርሃኑ ንጉሤ አንተ የክርስቶስ ገንዘብ ስለሆንህ ስምህ ከዛሬ ጀምሮ አለቃ ነዋየ ክርስቶስ ተብለህ ትጠራለህ።
አንተ የክርስቶስ ገንዘብ ስለሆንህ ስምህ ከዛሬ ጀምሮ አለቃ ነዋየ ክርስቶስ ተብለህ ትጠራለህ።
 
 

 
 
ፍቅሩ ኪዳኔ በ50ዎቹና በ60ዎቹ የአዲስ አበባ በግዜው ተወዳጅ የነበሩ ቦታዎቿን እና ልጆችዋን የሚያስታውስ ግሩም የሆነ መጽሐፍ።
በ50ዎቹና በ60ዎቹ የአዲስ አበባ በግዜው ተወዳጅ የነበሩ ቦታዎቿን እና ልጆችዋን የሚያስታውስ ግሩም የሆነ መጽሐፍ።
 
 
 
ብርሃኑ አባዲ ሃይላይ ሐድጉ እንደፃፈው ብርሃኑ አባዲ ከትግሪኛ ወደ አማርኛ እንደተረጎመው።
ሃይላይ ሐድጉ እንደፃፈው ብርሃኑ አባዲ ከትግሪኛ ወደ አማርኛ እንደተረጎመው።

 
 
 
መስፍን ወልደማርያም ኢትዮጵያዊነት ከአገዛዝ ሥርዓት ተለይቶ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው።
ኢትዮጵያዊነት ከአገዛዝ ሥርዓት ተለይቶ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው።
 
ዮሐንስ አድማሱ ዮፍታሔ ንጉሴ፣ ብሔረ ነገዱ፣ ሀገረ ሙላዱ፣ ጎጃም፤ ቅኔ የተቀኘበት፣ ድጓ የተማረበት፣ ምስጢር ያገመረበት ደብረ ኤልያስ ነበር። ጠይም ረዥም፤ ጠጉረ ሉጫ፤መልከ መልካም የቆንጆ ጠር፤ ቀጭን ዠርጋዳ ጣተ መልካም ፤ሽቅርቅር ጥዩፍ፤ ኮከቡ ሚዛን ነፋስ ነበር። ምዕ.1

ዮፍታሔ የቀለም ትምህርቱን ከመጀመሩ አስቀድሞ ምግበ አእምሮው የሆነውን የኤልያስን አየር እየተመገበ፣ ዝንጀሮ ያልቸውን ሁሉ ዘፈኑን፣ ስለምኑን፣ቁም ነገሩን፣ ወዘበሬታውን፣ ተረቱን፣ድርሳነ ባልቴቱን፣ ቀረርቶውን፣ልቅሶውን፣እማ በራዩን፣ ሙሻሙሾውን፣አይኮሉን፣ አረቦኑን፣ ወዘተ... እየሰማ ነበር ያደገው። ይኽ ሁሉ ኋላ ለተቀኘው ቅኔና ለደረሰው መዝሙር፣ ቲያትርና ስለምን ዐይነተኛ ዳራ ሁኖታል። ምዕ.1
የቅኔ ትምህርተ ተራውና ደረጃው ከፀዋትወ ዜማ ቀጥሎ ከትርጓሜ መጻሕፍት አስቀድሞ በጉልምስና ወራት ነው። ... ቅኔ የንባብና የጸዋትወ ዜማ ደጀን የትርጓሜ መጻሕፍት ፊታውራሪ ነው። ... ቅኔን ከጸዋትዋ ዜማ በፊት ከትርጓሜ መጻሕፍት በኋላ ለመማር በፍጹም አይቻልም። ይኽውም ከዘር በፊት ቡቃያ ከባል በፊት ልጅ ይሆናል።
የቅኔ ትምህርት...የትውልድ አገርን ትቶ ጋራ ዙሮ፣ ወንዝ ተሻግሮ ወጥቶ ወርዶ፣ከውሻ ተከላክሎ ፣ቁራሽ እንጀራ ለምኖ ፣ ደበሎና ማቅ ለብሶ፣ ተዋርዶ ተንከራትቶ፣ ብዙ ፈተና ተቀብሎ፣ አይመስሉ መስሎ፣ ቀይ የነበረው ጠቁሮ፣ ረዥም የነበረው አጥሮ፣ተርቦ ተጠምቶ ፣ ፀዋትወ መከራውን ሁሉ ታግሶ የሚማሩት የተባሕት ትምህርት ነው። " ምዕ.1፤ አለቃ ዕንባቆም ቃለ ወልድን ጠቅሶ"
... በዚህ ጥናት አማካይነት ዮፍታሔ ንጉሴን ለአንባቢው ለማቅረብ የሞከርሁት፣ የተቻለኝን ያህል፣ እንደሰው ነው-አለ አግባቡ እንዳይወደስ፣ አለ መልኩ እንዳይወቀስ ፣እንደ ግዕዙ እንዲታይ ነው። "ዮሐንስ"
"አፋጀሽኝ" ለአቶ ዮፍታሔ የመጀመሪያ ወይም የመጨረሻ ድርሰታቸው አንዳልሆነ መናገር የሚያሻ አይመስለኝም። ከሺ928 ዓ.ም. በፊት በልዩ ልዩ መሥጢራት የተቀመሙና የዝማሬ ጣእማቸው የሰሚን ሕሊና በሚመስጥ ዜማ የተቃኙ 16 ያህል ቲያትሮችና መዝሙሮች አዘጋጅተው በየጊዜው ለሕዝብ /በ/ማሳየታቸው የቲያትርና የድርሰት ሊቅነታቸው በሰፊው የታወቀ ሆኗል። አቶ በለጠ ገብሬ ፤ ሰንደቅ አላማችን /ሐምሌ 21፤ 1940 ካተመው ዮፍታሔ ከዚሕ ዓለም በሞት በተለየ ጊዜ እሱን ለመዘከር ከአደረጉት ንግግራቸው የተጠቀሰ።
ጠዋት ገረዳቸው ልትቀሰቅሳቸው ብታንኳኳ አልሰሙም። እንደገና አንኳኳች፤ አልሰሙም። ሰአት አለፈ። በኋላ ለፓርላማ ነገረች። ፖሊሶች መጡ። መጀመሪያ በሩን ሰብሮ የገባው ሻምበል ጎሹ ይመር፣ የፓርላማ የዘበኞች አለቃ፣ ነበር። ጠዋት ገና ነፍሳቸው አልወታም ነበር። ሲወራጩ ነበር ያደሩት። አንሶላው ፣ብርድ ልብሱ ተበታትኗል። ጧት ዐረፉ። ለአውቶፕሲ ያን ጊዜ ይኽ ምን እንደሆነ አላውቅም ነበር። ካዛፓፓላፊ ዋናው ላቦራቷር የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ላቦራቷረቸ ወሰድናቸው፤ አስታውኳቸው ነበር፤ አረንጓዴ ነበር መልኩ ትውከት፤ የከሰል ጢስ ነበር አፍኖ የገደላቸው። አቶ በለጠ ገብሬን ጠቅሶ

"ኮከብ እምኮከብ የኄይስ ክብሩ" የሚል የኖረ የግዕዝ አባብል አለ። አንዱ ኮከብ በብርሃኑ፣ በግዘፉ በጠቅላላ ተፈጥሮው ከሌላው ኮከብ ይበልጣል። እኔን የሚያስገርመኝ ይኽ አይደለም። አንዳንድ ከዋክብት አሉ እኛ በተለየ አጠራር ተወርዋሪ የምንላቸው። በሌሊቱ ኅዋ ውስጥ ከአንዱ ማዕዘን ሰማይ ወደ ሌላው ተወርውረው ብልጭ ብለው ይጠፋሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው በቅጽበት ነው። ያንን በጨለማው ግርማ የተዋጠውን ኅዋ በብርሃን ጎርፍ ሰንጥቀው አጥለቅልቀውት ይጠፋሉ። ተመልካችም ከመገረም በሚመነጭ ዝምታ ይዋጣል። በኢትዮጵያም የሥነ ጽሑፍ ኅዋ ውስጥ ዮፍታሔ ንጉሤ አንድ ታላቅ ተወርዋሪ ኮከብ ነበር።... ዮሐንስ መነን፤ ሰኔ 25 1961 ዓ.ም. ላይ ባወጣው ለማስታወስ ያህል ከሚለው ጽሑፉ ራሱ የጠቀሰው--አሰናኙ።
ያስጨነቅቸው እመቤቱ በተመለሰች በስድስተኛው ዓመት እሱ ደግሞ በፈንታው፣ የፈንታውን እስከ ለመቼውም ላይመለስ ሄደ። እመቤቱ ምን አደረገችለት? እኛ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ በ1887-1939። ዮሐንስ የመጀመሪያውንክፍል የሸባበት /በሱው ቋንቋ/፤ ማጣቀሻዋ የዮፍታሔ "ድንግል ሀገሬ ሆይ" የምትለው መዝሙር ናት--አሰናኙ።

ድንግል ሀገሬ ሆይ ጥንት ተደንግሎ
ሕፃናቱም ታርደው ያንችም ልብ ቆስሎ
ልጅሽ ተሰደደ አንቺን ተከትሎ
የሕፃናቱን ደም አዘክሪ ኩሎ።
አስጨነቀኝ ስደትሺ
እመቤቴ ተመለሺ ተመለሺ።
"ድንግል ሀገሬ ሆይ"


ትምህርት እንዲስፋፋ ጉልበት እንዲጠና
አራቱ ጉባኤ ይነሡልንና
መኮንን ደረሶ አሉላ ጎበና
አገራችን ትማር አሁን እንደገና።
ጎበና
ከፈረስህ ጋራ ተነስ እንደገና።
አጥንቱን ልልቀመው
ዮፍታሔ ንጉሴ፣ ብሔረ ነገዱ፣ ሀገረ ሙላዱ፣ ጎጃም፤ ቅኔ የተቀኘበት፣ ድጓ የተማረበት፣ ምስጢር ያገመረበት ደብረ ኤልያስ ነበር። ጠይም ረዥም፤ ጠጉረ ሉጫ፤መልከ መልካም የቆንጆ ጠር፤ ቀጭን ዠርጋዳ ጣተ መልካም ፤ሽቅርቅር ጥዩፍ፤ ኮከቡ ሚዛን ነፋስ ነበር። ምዕ.1

ዮፍታሔ የቀለም ትምህርቱን ከመጀመሩ አስቀድሞ ምግበ አእምሮው የሆነውን የኤልያስን አየር እየተመገበ፣ ዝንጀሮ ያልቸውን ሁሉ ዘፈኑን፣ ስለምኑን፣ቁም ነገሩን፣ ወዘበሬታውን፣ ተረቱን፣ድርሳነ ባልቴቱን፣ ቀረርቶውን፣ልቅሶውን፣እማ በራዩን፣ ሙሻሙሾውን፣አይኮሉን፣ አረቦኑን፣ ወዘተ... እየሰማ ነበር ያደገው። ይኽ ሁሉ ኋላ ለተቀኘው ቅኔና ለደረሰው መዝሙር፣ ቲያትርና ስለምን ዐይነተኛ ዳራ ሁኖታል። ምዕ.1
የቅኔ ትምህርተ ተራውና ደረጃው ከፀዋትወ ዜማ ቀጥሎ ከትርጓሜ መጻሕፍት አስቀድሞ በጉልምስና ወራት ነው። ... ቅኔ የንባብና የጸዋትወ ዜማ ደጀን የትርጓሜ መጻሕፍት ፊታውራሪ ነው። ... ቅኔን ከጸዋትዋ ዜማ በፊት ከትርጓሜ መጻሕፍት በኋላ ለመማር በፍጹም አይቻልም። ይኽውም ከዘር በፊት ቡቃያ ከባል በፊት ልጅ ይሆናል።
የቅኔ ትምህርት...የትውልድ አገርን ትቶ ጋራ ዙሮ፣ ወንዝ ተሻግሮ ወጥቶ ወርዶ፣ከውሻ ተከላክሎ ፣ቁራሽ እንጀራ ለምኖ ፣ ደበሎና ማቅ ለብሶ፣ ተዋርዶ ተንከራትቶ፣ ብዙ ፈተና ተቀብሎ፣ አይመስሉ መስሎ፣ ቀይ የነበረው ጠቁሮ፣ ረዥም የነበረው አጥሮ፣ተርቦ ተጠምቶ ፣ ፀዋትወ መከራውን ሁሉ ታግሶ የሚማሩት የተባሕት ትምህርት ነው። " ምዕ.1፤ አለቃ ዕንባቆም ቃለ ወልድን ጠቅሶ"
... በዚህ ጥናት አማካይነት ዮፍታሔ ንጉሴን ለአንባቢው ለማቅረብ የሞከርሁት፣ የተቻለኝን ያህል፣ እንደሰው ነው-አለ አግባቡ እንዳይወደስ፣ አለ መልኩ እንዳይወቀስ ፣እንደ ግዕዙ እንዲታይ ነው። "ዮሐንስ"
"አፋጀሽኝ" ለአቶ ዮፍታሔ የመጀመሪያ ወይም የመጨረሻ ድርሰታቸው አንዳልሆነ መናገር የሚያሻ አይመስለኝም። ከሺ928 ዓ.ም. በፊት በልዩ ልዩ መሥጢራት የተቀመሙና የዝማሬ ጣእማቸው የሰሚን ሕሊና በሚመስጥ ዜማ የተቃኙ 16 ያህል ቲያትሮችና መዝሙሮች አዘጋጅተው በየጊዜው ለሕዝብ /በ/ማሳየታቸው የቲያትርና የድርሰት ሊቅነታቸው በሰፊው የታወቀ ሆኗል። አቶ በለጠ ገብሬ ፤ ሰንደቅ አላማችን /ሐምሌ 21፤ 1940 ካተመው ዮፍታሔ ከዚሕ ዓለም በሞት በተለየ ጊዜ እሱን ለመዘከር ከአደረጉት ንግግራቸው የተጠቀሰ።
ጠዋት ገረዳቸው ልትቀሰቅሳቸው ብታንኳኳ አልሰሙም። እንደገና አንኳኳች፤ አልሰሙም። ሰአት አለፈ። በኋላ ለፓርላማ ነገረች። ፖሊሶች መጡ። መጀመሪያ በሩን ሰብሮ የገባው ሻምበል ጎሹ ይመር፣ የፓርላማ የዘበኞች አለቃ፣ ነበር። ጠዋት ገና ነፍሳቸው አልወታም ነበር። ሲወራጩ ነበር ያደሩት። አንሶላው ፣ብርድ ልብሱ ተበታትኗል። ጧት ዐረፉ። ለአውቶፕሲ ያን ጊዜ ይኽ ምን እንደሆነ አላውቅም ነበር። ካዛፓፓላፊ ዋናው ላቦራቷር የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ላቦራቷረቸ ወሰድናቸው፤ አስታውኳቸው ነበር፤ አረንጓዴ ነበር መልኩ ትውከት፤ የከሰል ጢስ ነበር አፍኖ የገደላቸው። አቶ በለጠ ገብሬን ጠቅሶ

"ኮከብ እምኮከብ የኄይስ ክብሩ" የሚል የኖረ የግዕዝ አባብል አለ። አንዱ ኮከብ በብርሃኑ፣ በግዘፉ በጠቅላላ ተፈጥሮው ከሌላው ኮከብ ይበልጣል። እኔን የሚያስገርመኝ ይኽ አይደለም። አንዳንድ ከዋክብት አሉ እኛ በተለየ አጠራር ተወርዋሪ የምንላቸው። በሌሊቱ ኅዋ ውስጥ ከአንዱ ማዕዘን ሰማይ ወደ ሌላው ተወርውረው ብልጭ ብለው ይጠፋሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው በቅጽበት ነው። ያንን በጨለማው ግርማ የተዋጠውን ኅዋ በብርሃን ጎርፍ ሰንጥቀው አጥለቅልቀውት ይጠፋሉ። ተመልካችም ከመገረም በሚመነጭ ዝምታ ይዋጣል። በኢትዮጵያም የሥነ ጽሑፍ ኅዋ ውስጥ ዮፍታሔ ንጉሤ አንድ ታላቅ ተወርዋሪ ኮከብ ነበር።... ዮሐንስ መነን፤ ሰኔ 25 1961 ዓ.ም. ላይ ባወጣው ለማስታወስ ያህል ከሚለው ጽሑፉ ራሱ የጠቀሰው--አሰናኙ።
ያስጨነቅቸው እመቤቱ በተመለሰች በስድስተኛው ዓመት እሱ ደግሞ በፈንታው፣ የፈንታውን እስከ ለመቼውም ላይመለስ ሄደ። እመቤቱ ምን አደረገችለት? እኛ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ በ1887-1939። ዮሐንስ የመጀመሪያውንክፍል የሸባበት /በሱው ቋንቋ/፤ ማጣቀሻዋ የዮፍታሔ "ድንግል ሀገሬ ሆይ" የምትለው መዝሙር ናት--አሰናኙ።

ድንግል ሀገሬ ሆይ ጥንት ተደንግሎ
ሕፃናቱም ታርደው ያንችም ልብ ቆስሎ
ልጅሽ ተሰደደ አንቺን ተከትሎ
የሕፃናቱን ደም አዘክሪ ኩሎ።
አስጨነቀኝ ስደትሺ
እመቤቴ ተመለሺ ተመለሺ።
"ድንግል ሀገሬ ሆይ"


ትምህርት እንዲስፋፋ ጉልበት እንዲጠና
አራቱ ጉባኤ ይነሡልንና
መኮንን ደረሶ አሉላ ጎበና
አገራችን ትማር አሁን እንደገና።
ጎበና
ከፈረስህ ጋራ ተነስ እንደገና።
አጥንቱን ልልቀመው
 
| ወደፊት >> 
   
       

መጸሐፍ ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ

ተመዝግበው ከሆነ እዘህ ይጫኑ
 

መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com