የብላቴን ጌታ ፀጋዬ ገብረመድህን ምርጥ የግጥም ስብስብ የያዘ መድብል ነው።
|
|
|
ከመጽሐፉ የተወሰደ
“ሰው ሀብታም ሆነ ደሀ ልዩነቱ የሚታየው በዝቅተኛ የዕውቀት እና የእምነት ደረጃ እስካለ ድረስ ብቻ ነው። ወደ ላይ ከፍ ካሉ በኋላ ወደ ፍጹምነት ደረጃ ሲደርሱማ የሚያስቡለት የሚሰስቱለት ነገር አይሆንም። እዚህ ከፍታ ላይ ያለ ሰው ብዙ ቢኖረው አይተርፈውም። ስለሚያካፍል፤ ትንሽም ያለው አያንሰውም። ብዙ ስለማይፈልግ ነው። ወደዚህ ዓለም ይዞት የመጣው፣ ሲሔድም የሚያከትለው አንዳች ነገር አለመኖሩን ያውቃልና ነው”
ሀገር፣መንደር፣ቤት ንብረቱን ትቶ ወደ ሩቅ የሄደ ሰው ባይተዋር ይባላል። ይህ ስያሜ በኑሮ አድራሻ መለወጥ ብቻ ምክንያቱን የሚያገኝ አይደለም ።የመንፈስ ባይተዋርነትም አለ። ሰው ከነበረበት ቦታ ወደ ሌላ ሳይዘዋወርም ለአዲስ አስተሳተሰብ፣ ፈሊጥና የኑሮ መልክ ሊጋለጥ ይችላል።አንደኛው እስኪያይል ወይም ሁለቱም እስኪዋሐዱ ድረስ የወትሮው እና የአሁኑ በህሊና ውስጥ የባላንጣዎች ተቃርኖ ይፈጥራሉ። እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው የቸልተኝነት የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል። " አስመሳይ፤ አድር ባይ እንደ እምነቱ የማይኖር እንደ ኑሮው የማያምን የሕሊናውን ብኩርና ለምስር ንፍሮ የለወጠ" ሌላም ሌላም እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል። "የሞራል ድቀት" የሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራልን? የመነሳቱ፣ የመቆሙ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠብቆ የመራመዱ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።
|
|
|
የሃበሻ ጀብዱ የማይጨው ጦርነት ከዝግጅቱ እስከ መጨረሻ ፍልሚያው በነበሩ ኢትዮጵያን በግንባር ተገኝተው ይደግፉ በነበሩት ቼኮዝላቫኪያዊው አዶልፍ ፓርለሳክ የአይን እማኝነት የተጻፈ ነው ። የጦርነቱን አመጣጥና ዝግጅት እያስቃኘ የሃበሻን ወደር የለሽ ጀግንነት፣ አምላኩን ወዳጅ፣ ሀገሩንና ሃይማኖቱን አጥብቆ አክባሪ ታማኝ እና ለክብሩ ሟች እንደሆነ የሚመሰክር መጽሐፍ ነው።
|
|
|
An eighteen-year old girl sets out to meet a young man who she had never met before and is swept away by a series of events that transformed her life in a way she could have never imagined. Tower in the sky is the story of love, revolution, hopes, dreams, violence, terror, trust, betrayal, tragedy, disillusionment, self-transformation and the triumphal power of the human spirit. The book vividly depicts a moment in Ethiopia’s history when the country convulsed with violence unleashed by a bloodthirsty military government that massacred an untold number of people, especially the young and plunged the country into darkness. It is also the story of thousands of young people who stood up against one of the most brutal dictatorships in history and fought for equality, freedom, social justice, and dignity.
|
|
|