የኢትዮጵያ ደራስያን በፊደል ማውጫ
 
Members Login
Your Email/Username
Password:
 

New member? Sign up!

Forgot password?

 
ጦማር
 
ስለኢትዮጵያ፡ደራሲያን።
ጽሑፉ፡የፕሮፌሰር፡ታምራት፡አማኑኤል፡ነው። ፕሮፌሰር፡ታምራት፡ከዛሬ፡ኻያዐምስት፡ዓመታት፡በፊ ት፡በትምርትና፡ሥነጥበብ፡ሚኒስቴር፡አማካሪ፡ኾነው ይሠሩ፡ነበር።ነገር፡ግን፡በዚያን፡ጊዜ፡ፕሮፌሰር፡በ መባል፡ፈንታ፡ሊቀማእምራን፡ይባሉ፡ነበር።
የልብ ወለድ ሥነጽሑፍ ጉዞ
ሥነ ጽሑፍ ጠቅላላ ዓላማው ማስደሰት ነው። ይህንንም ጉልህ አላማ የሚፈጽመው ሁሉን አቀፍ የሕይወት ኂስ በማቅረብ ነው። ሥነ ጽሑፍ ጉልህ ዓላማውን ለመፈጸም ጥራትና ወጥነት እንዲኖረው ያስፈልጋል።" በኑኀ ዘመን ፥ በቀን ብዛት የማይነቅዝና የማይሻግት" መሆን አለበት። አለበለዚያ አጉል ጒህና ወይም ብስና እንጂ ሥነ ጽሑፍ ሊሆን አይችልም።
ዶ/ር እጓለ ገብረዮሐንስ፤ በ‹‹ የሠዓሊ ገብረ ክርስቶስ ደስታ የመጀመሪያ የሥዕል ትርኢት ካታሎግ ፲፱፻፶፮ ዓ.ም ›› ላይ ያቀረቡት የመግቢያ ጽሑፍ።
ይህ ደራሲ እንደሚለው ሰው ከሌሎቹ ሕያዋን የሚለይበት ዋናው ምልክት ጥበብ የምንለው ነው። የተሳሳተ አይመስለኝም። ፈረንጆችን የጥበብን ባሕርይ በሚገባ ስለሚረዱ ሌላ መግለጫ ዘዴ ቢያጡ የጥበበኛውን የሥራ ጠባይ ከፈጣሪነት ጋር አስተካክለው ይናገራሉ። በሀገራችን የሐሳብ ዘዴ ፈጣሪነት ከመለኮት ጋር ብቻ የተያያዘ ነው።
 
አጭር ልብ ወለድ
 
THE QUEEN OF SHEBA'S NIGHTMARE
The Queen of Sheba, returning from her visit to King Solomon, was riding through the desert on a white ass with her Grand Vizier beside her on an ass of more ordinary colour. As they rode, she discoursed reminiscently about the wealth and wisdom of Solomon.
ቱሉ ፎርሣ
ቱሉን ማን የማያውቅ አለ ? እናንተ አታውቁትም እንዴ ? ቱሉ ይኼ ማካሮኒ ፋብሪካ የሚሠራው እኮ ነው፡፡ ኦ ! ቱሉን የማያውቅ ማን አለ ቱሉ ሠላሳ አንድ ዓመቱ ነው።ወይም ወደዚያ ግድም ነው። እና ቱሉ ቁመቱ ረጅም ነው። የቱሉ እጆች ትላልቅ ናቸው።የቱሉ ክንዶች ጠንካሮች ናቸው።የቱሉ መዳፎች ሸካራ ናቸው። ቱሉ ከማካሮኒ ፣ፓስታና ፓስቲኒ ፋብሪካ ውስጥ ወፍጮ ክፍል ነው የሚሠራው። ወፍጮ ክፍል ስድስት ዓመት ሠርቷል።
THE DISTRICT DOCTOR
One day in autumn on my way back from a remote part of the country I caught cold and fell ill. Fortunately the fever attacked me in the district town at the inn I sent for the doctor. In half-an-hour the district doctor appeared, a thin, dark-haired man of middle height. He prescribed me the usual sudorific, ordered a mustard-plaster to be put on, very deftly slid a five-ruble note up his sleeve, coughing drily and looking away as he did so, and then was getting up to go home, but somehow fell into talk and remained

 


 

 

 
   
 
ሊነበቡ የሚገባቸው 10 ምርጥ የታሪክ መጻሕፍት
ሊነበቡ የሚገባቸው 10 ምርጥ ልቦለድ ድርሰቶች
ሊነበቡ የሚገባቸው 10 ምርጥ የግጥም መድብሎች
   

 

መጽሐፍ መፈለጊያ/Search Books
 
 
 
   
 
ተጨማሪ የምርምር ጽሑፎችን ለማግኘት እዚህ ይጫኑ

በቅርቡ በገበያ ላይ የዋሉ አዳዲስ መጻሕፍት
ስለወቅቱ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁኔታ አንዳንድ ማስታወሻ
ምርጥ አጫጭር ታሪኮች
ተዎድሮስ:ሰሐቀ:እምነ:ሰማይ:መንበሩ፣
አመ:በዓደኑ:ነደረ:አክሊሎ: እንዘ:ደትቄደሎ:አረሩ።

ታከለ ወልደሀዋርያትን ከአብዛኛው ሰው የሚለየው ጠባይ ቢኖር ዛሬ ስለተሸነፈ ትግሉን ያለማቋረጡ ነው። ልጅ እያሱን ለኢትዮጵያ አይበጅም ብሎ ባመነበት ሰአት ልጅእያሱን ለማስወገድ በሙሉ ልቦናውና በሙሉ አቅሙ ታገለ። ...አሁን ደግሞ ተፈሪ ማለፍአለበት ነገር ግን ተፈሪን እጥላለሁ ማለት ኢትዮጵያን እስካልጎዳ ድረስ ብቻ ነው። ምክንያቱም ተፈሪ ያልፋል፣ታከለም ያልፋል፣ የምትዘልቀው ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ስለዚህም የታከለ አላማ እስከ ህይወቱ መጨረሻ ድረስ የሚከተለው ይሆናል።
ከመጽሐፉ የተወሰደ
ሕብረት ባጣ የኃላፊነት ሥራ ለሹመት፣ለመወደድ ሲባል በሚደረግ ሩጫ መካከል ሰሚ የሚያጡ ማህበራዊ ችግሮች እየተደመሩ የሕዝብ እሮሮና ጩኸቶች እየበረከቱ፣ በደሎች እየወፈሩን እየሰፉ፣ እድገታቸውም ተመንድጎ እየወጣ መመለሻና መቃኛ ከሌለው ችግር ውስጥ ተዘፍቀው ይቀራሉ። ጦሳቸውም ከትውልድ እስከ ትውልድ ተላላፊ በሽታ ይሆናል።
አገርን ለመምራት የታደሉና የተመረጡ መሪዎችና ሹሞች አልሚነትና አጥፊነታቸውን ሕዝብን መስተዋታቸው አድርገው እራሳቸውን መመልከት ቢችሉ፣ ሕዝብ በመስተዋትነቱ ከእምነት ስለማይርቅባቸው አገር መልጽጋ ፣ ፍትህና ርትዕ ነግሦ፣ የአገር መሬት ፍሬዋን ሰጥታ መክበሪያና መጠቀሚያ እንጂ መቀበሪያ ብቻሆና ዜጎቿን አታስተናግድም።
ስለ መጽሐፉ የቀረበውን ሙሉ ቅኝት ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
 
         

በቅርቡ በድጋሚ የታተሙ ቀደምት መጻሕፍት
ከስብሃት የምንጊዜም ምርጥ ድርሰቶች እናትን እንዲሁም አምስት ስድስት ሰባት የተካተቱበት።
የዚህ : የታሪክ : ማስታወሻ : ረቂቅ : የጻፍሁት : በ፲፱፻፴ : ዓ.ም : ኢየሩሳሌም : ላይ : በስደት : ሳለሁ : ነበር፤ የኢትዮጵያ : የነጻነት :ጮራ : በፈነጠቀበት : ጊዜ : ቀዳሚ : መልክተኛ : ሆኜ : በሱዳን : በኩል : ወደ : ኢትዮጵያ : በገባሁ : ጊዜ : ረቂቁ : ከጓዝ : ጋር : ቋራ : ላይ : ቀርቶ : ነበርና : ጠፋብኝ። ቢሆንም፤ ታሪኩ : በአእምሮዬ : ውስጥ : ተቀርጾ : ሁል : ጊዜ : ትዝ : ይለን : ስለነበር : በ፲፱፻፴፱:ዓ.ም : የዚህን : ማስታወሻ : ረቂቅ : በድጋሚ : ጻፍኩት።
ስለ መንግስቱ ለማ አንዳንድ ሰዎች በጣም የተሳሳተ አመለካከት አላቸው፤ ወግ-አጥባቂና ትምክህተኛ ይመስላቸዋል። ግን አልነበረም።... ዘረኝነት የሚባል ነገር በተለይ ሲያልፍም አይነካው። በአስተሳሰቡ ከጊዜ የቀደመ ... የዛሬና የነገ ሰው ነው። እርግጥ ለባህል መጠበቅ አጥብቆ ይቆረቆራል።
         

አንባብያን ቢያነቧቸው የሚመከሩ መጻሕፍት
የብላቴን ጌታ ፀጋዬ ገብረመድህን ምርጥ የግጥም ስብስብ የያዘ መድብል ነው።
ከመጽሐፉ የተወሰደ
“ሰው ሀብታም ሆነ ደሀ ልዩነቱ የሚታየው በዝቅተኛ የዕውቀት እና የእምነት ደረጃ እስካለ ድረስ ብቻ ነው። ወደ ላይ ከፍ ካሉ በኋላ ወደ ፍጹምነት ደረጃ ሲደርሱማ የሚያስቡለት የሚሰስቱለት ነገር አይሆንም። እዚህ ከፍታ ላይ ያለ ሰው ብዙ ቢኖረው አይተርፈውም። ስለሚያካፍል፤ ትንሽም ያለው አያንሰውም። ብዙ ስለማይፈልግ ነው። ወደዚህ ዓለም ይዞት የመጣው፣ ሲሔድም የሚያከትለው አንዳች ነገር አለመኖሩን ያውቃልና ነው”
ሀገር፣መንደር፣ቤት ንብረቱን ትቶ ወደ ሩቅ የሄደ ሰው ባይተዋር ይባላል። ይህ ስያሜ በኑሮ አድራሻ መለወጥ ብቻ ምክንያቱን የሚያገኝ አይደለም ።የመንፈስ ባይተዋርነትም አለ። ሰው ከነበረበት ቦታ ወደ ሌላ ሳይዘዋወርም ለአዲስ አስተሳተሰብ፣ ፈሊጥና የኑሮ መልክ ሊጋለጥ ይችላል።አንደኛው እስኪያይል ወይም ሁለቱም እስኪዋሐዱ ድረስ የወትሮው እና የአሁኑ በህሊና ውስጥ የባላንጣዎች ተቃርኖ ይፈጥራሉ። እንዲህ ያለ ሰውነት ሲታገል ይቆይና ሲሰለቸው የቸልተኝነት የግዴለሽነት ኢንዲፈረንቲዝም መንፈስ ይሰፍንበታል። ይህ በተለይ የሚገለጸው በሥነ ምግባር መስክ ነው። ሥለታም የነበረው ሥነ ምግባራዊ በሕሊናው ይሰንፋል። የሚመቹ፣ የማይቆረቁሩ፣ የማይጋጩ እንደ ዘዴኝነት፣ ጮሌነት፣ ብልሃተኝነት ያሉ የማይጨበጡ የቀልጣፋ ሰውነት ጠባዮች ያይላል። " አስመሳይ፤ አድር ባይ እንደ እምነቱ የማይኖር እንደ ኑሮው የማያምን የሕሊናውን ብኩርና ለምስር ንፍሮ የለወጠ" ሌላም ሌላም እንደ አለንጋ የሚጋረፉ ተግሣጾች ወቅታዊነታቸውን የሚያገኙት በዚህ ሳቢያ ይመስለናል። "የሞራል ድቀት" የሚባለው ይህ ሳይሆን ይቀራልን? የመነሳቱ፣ የመቆሙ ከራሱ ጋር ተስማምቶ ሚዛን ጠብቆ የመራመዱ ነገርስ እንዴት ይሆን? ቅን ሕሊና የማያልፈው ጥያቄ ነው።
የሃበሻ ጀብዱ የማይጨው ጦርነት ከዝግጅቱ እስከ መጨረሻ ፍልሚያው በነበሩ ኢትዮጵያን በግንባር ተገኝተው ይደግፉ በነበሩት ቼኮዝላቫኪያዊው አዶልፍ ፓርለሳክ የአይን እማኝነት የተጻፈ ነው ። የጦርነቱን አመጣጥና ዝግጅት እያስቃኘ የሃበሻን ወደር የለሽ ጀግንነት፣ አምላኩን ወዳጅ፣ ሀገሩንና ሃይማኖቱን አጥብቆ አክባሪ ታማኝ እና ለክብሩ ሟች እንደሆነ የሚመሰክር መጽሐፍ ነው።
An eighteen-year old girl sets out to meet a young man who she had never met before and is swept away by a series of events that transformed her life in a way she could have never imagined. Tower in the sky is the story of love, revolution, hopes, dreams, violence, terror, trust, betrayal, tragedy, disillusionment, self-transformation and the triumphal power of the human spirit. The book vividly depicts a moment in Ethiopia’s history when the country convulsed with violence unleashed by a bloodthirsty military government that massacred an untold number of people, especially the young and plunged the country into darkness. It is also the story of thousands of young people who stood up against one of the most brutal dictatorships in history and fought for equality, freedom, social justice, and dignity.
         
         
50 አመት ያለፋቸው እንዲሁም የደራሲያን መልካም ፈቃድ የተሰጠባቸው ለአንባብያን እንዲደርሱ በሶፍት ኮፒ የተገኙ።

ከመጸሃፉ የተወሰደ የጎመን ዘር ቢዘሩት ሰናፍጭ አይሆንም ሰውንም አንተ ባሪያ አንተ ጋላ ብሎ ቢሰድቡት የአዳም ልጅ መሆኑን አይተውም። መልካም ቆንጆ አመንዝራ ሴት ካልች በት ቤት አትግባ በከንቱ እንዳትሞት። ሴት ከመሆን ወንድ መሆን ይሻላል። እንስሰ ከመሆን ሰው መሆን ይሻላል። ደንቆሮ ከመሆን ብልህ መሆን ይሻላል።
የዐፄ ምኒሊክ ዘመን በወጣቱ አስኳላ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ አስመራ ፩፱፲፩፪።
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ከግእዝ ወደአማርኛ ከመለሷቸው ጥንታዊ የስነጽሁፍ ቅርሶች አንዱ።

ትልቁን የስዋስው መጽሐፍ መጻፍ ከመጀመራቸው በፊት መንደርደሪያ እንዲሆናቸው የጻፉት መጽሐፍ ነው።

የኢትዮጵያ ሕገመንግሥት ነሃሴ 1987ዓ.ም የፀደቀው።

ይህ በኒዘርላንድ ናኖ ሕትመትን በመጠቀም ሊሠራ የታሰበው የብረት ድልድይ የኮምፒዩተር ምስል ነው። ሁለቱ ሮቦቶች ከየወገናቸው የብረት ድልድዩን ካለደጋፊና መወጣጫ እያተሙ ሁለቱም ያጠናቅቁ የድልድዩ ሁለት ወገኖች ይገጥማሉ። በዚህ በፎቤስ መጽሔት በናንሲ አዋኖ በቀረበ ጽሑፍ በ2008 (20017 እኤአ) የደች መሃንዲስ ላርማን ሁለቱን ሮቦቶች በካናሉ ላይ አድርጎ ካስነሳ በኋላ በሁለት ወሩ ተመልሶ ሲመጣ የሰው መሸጋገሪያ ድልድዩ ተገባዶ ለመገልገያነት ተዘጋጅቶ ይጠብቀዋል።
         
በየመጻሕፍት መደብሮች የሚገኙ አዳዲስ መጻሕፍት
         
         
የዚህ ድረ-ገጽ መሠረታዊ ይዘቶች የተቃኙት በ
<< ያሠርቱ ምእት ፥ የብርእ ምርት ( ከ፲፻ እስከ ፳፻ ) ድርሰት ክፍል ፩
ጳጉሜን ፫ ቀን ፲፱፻፺፱ ዓ.ም በብርሃነመስቀል ደጀኔ 'ና
ጌታሁን ሽብሩ >>
በተዘጋጀው ያልታተመ ጥናታዊ ጽሑፍ ነው።