[
ዋና ገጽ
|
ስለኛ
|
አስተያየት
|
አድራሻችን
]
ታሪክ
|
ምርምርና ጥናት
|
ልቦለድ
|
ግጥምና ቅኔ
|
ተውኔት
|
ትምህርት
|
ፍልስፍና
|
ተረቶችና ቀልዶች
|
ትርጉም
|
ወግ
|
መንፈሳዊ ድርሰቶች
|
መዛግብተ-ቃላት
የኢትዮጵያ ደራሲያን በፊደል ማውጫ
አ
በ
ቨ
ገ
ደ
ጀ
ሀ
ወ
ዘ
ዠ
ሐ
ኀ
ጠ
ጨ
የ
ከ
ኸ
ለ
መ
ነ
ኘ
ሠ
ዐ
ፈ
ጸ
ፀ
ቀ
ረ
ሰ
ሸ
ተ
ቸ
ጰ
ፐ
ወደ ዋና ገጽ
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አሐዱ ሳቡሬ Ahadu Sabure
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አለማየሁ ገላጋይ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1674 - 1699]
ዐፄ አድያም ሰገድ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አእምሮ ወንድምአገኝ Aemro Wondemagegne
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1930 - 1990]
ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ Pro. Ashenafi Kebede
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አባ አካለ ክርስቶስ Akale Kiristose
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አሕመዲን ጀበል
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አያሌው ታምሩ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አሰፋ ጫቦ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አክሊለብርሃን ወልደቂርቆስ Aklileberhane Woldekirkos
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አሳምነው ገብረወልድ Asamnew Gebrewold
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አንዳርጋቸው አሰግድ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አቤ ጉበኛ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አቤ ጉበኛ በ፲፱፳፭ ዓ.ም. በባሕር ዳር ከተማ ተወለዱ፡፡ በስድስት ዓመታቸው ፊደል ቆጥረው ንባብ ተማሩ፡፡ ቀጥሎም የቤተክርስቲያን ትምህርት ተከታተሉ፡፡ ከዚያም ወደ ዳንግላ ሄደው ቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ተብሎ ይጠራ በነበረ ትምህርት ቤት እስከ ስድስተኛ ክፍል ተማሩ። ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀቁ፡፡
አቤ ጉበኛ በመጀመሪያ ሥራ የጀመሩት ማስታወቂያ ማኒስቴር ቀጥሎ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ሲሆን በመንግሥት ሥራ ከስድስት ዓመት የበለጠ አልቆዩም፡፡ ሕይወታቸውን በአብዛኛው የገፉት በደራሲነት ነው፡፡ አቤ ጉበኛ ለትውልድ ቅርስ የሚሆኑ የተለያዩ ድርሰቶችን በአማርኛና በእንግሊዝኛ በመድረስ አባትመዋል፡፡ ካሳተሟቸው በርካታ መጽሐፎች በተጨማሪ “ቂመኛው ባሕታዊ” እና የ “ደካሞች ወጥመድ” የተባሉ ቲያትሮች አዘጋጅተው ለሕዝብ ታይተዋል፡፡
በአቤ ጉበኛ ብዕር ተከሽኖ የቀረበና በ፲፱፷፮ ዓ.ም. ዳግም ለኀትመት የበቃው እና አብዮቱ በሀገሪቱ ሲቀጣጠል በኀብረተሰቡ ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ የተነበበው “አልወለድም” የተሰኘው መጽሐፍ ማንም ሰው ከእናቱ ማሕጸን ጀምሮ ምኞትና ጥንቃቄ ሊለየው እንደማይገባ የሚያትት ሲሆን በመታየት ላይ ያለው እውነታ ግን አዳጋች የሆነና የሰው ዘር በድህነት ተወልዶ አድጎና ኑሮው በድህነት እንደሚያልፍ ያሳያል፡፡ እንዲህ ያለው ሁኔታ አግባብ አለመሆኑንም ይቃወማል፡፡
መጽሐፉ የሰው ልጅ የሚደርስበትን መከራ በመቃወም ይሞግታል፡፡ የሰው ልጅ መብት በአግባቡ መጠበቅ እንዳለበትም ያስረዳል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አቤ ጉበኛ በ፲፱፳፭ ዓ.ም. በባሕር ዳር ከተማ ተወለዱ፡፡ በስድስት ዓመታቸው ፊደል ቆጥረው ንባብ ተማሩ፡፡ ቀጥሎም የቤተክርስቲያን ትምህርት ተከታተሉ፡፡ ከዚያም ወደ ዳንግላ ሄደው ቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ተብሎ ይጠራ በነበረ ትምህርት ቤት እስከ ስድስተኛ ክፍል ተማሩ።
አየለ ተክለ ሃይማኖት
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አማረ ማሞ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አማረ ማሞ በ፲፱፴፱ ዓ.ም. በሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት በደረሰ ጊዜ ፊደል በመቁጠር ዳዊት ደግመዋል፡፡ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ የከፍተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለው በሥራ ዓለም በቀድሞው የምሥራች ድምፅ ውስጥ የሥነ ጽሑፍ ኃላፊ ሆነው ከማገልገላቸውም በተጨማሪ የትርጉም ሥራዎች ሠርተዋል።
አማረ ማሞ ለረጅም ዓመታት የኢትዮጵያ መጽሐፍት ድርጅት ም/ሥራ አስኪጅ በመሆን አገልግለዋል፡፡ የተለያዩ ድርሰቶችን በመድረስና የትርጉም ሥራዎችን በማዘጋጀት ከሰላሳ በላይ መጻሕፍት አሳትመዋል፡፡ ከ፲፱፷፮ ዓ.ም. በኋላም በርካታ ወይ ድርሰቶችንና የድርሰት መማሪያ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅተዋል። ከነዚህም መካከል በ፲፱፷፰ ዓ.ም. "የልብ ወለድ ድርሰት አጻጻፍ"፣ በ፲፱፸፮ ዓ.ም. "የቀለም ጠብታ" እና በ፲፱፹፬ ዓ.ም. "አሳረኛው"፣ በሚል የታተመው የትርጉም ሥራም ተጠቃሾች ናቸው። ለሀገራችን የሥነ ጽሑፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ደራስያን ማኀበር የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በመሆን አገልግለዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን መህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አማረ ማሞ በ፲፱፴፱ ዓ.ም. በሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት በደረሰ ጊዜ ፊደል በመቁጠር ዳዊት ደግመዋል፡፡ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ የከፍተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለው በሥራ ዓለም በቀድሞው የምሥራች ድምፅ ውስጥ የሥነ ጽሑፍ ኃላፊ ሆነው ከማገልገላቸውም በተጨማሪ የትርጉም ሥራዎች ሠርተዋል።
አሰፋ ገብረማርያም Asefa Gebremariam
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አሰፋ ገብረ ማርያም በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት በጨርጨር አውራጃ በሀብሮ ወረዳ መቻራ በምትባል አካባቢ ተወለዱ።
አሰፋ ገብረ ማርያም ከጣሊያን ወረራ በኋላ የሴተኛ አዳሪነት መስፋፋትን ችግር አስመልክቶ “እንደወጣች ቀረች” የሚል መጽሐፍ ጽፈዋል፡፡ በዚህም ስለሴተኛ አዳሪነት አደገኛ መሆኑንና መወገዝ እንዳለበት ግብረገባዊ በሆነ መንገድ አቅርበዋል፡፡ የመጀመሪያዋን እንደወጣች ቀረች የተባለችውን ልብወለድ የጻፉት በ፲፱፵፱ ዓ.ም. ነበር፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ ካሌንደር።
አሰፋ ገብረ ማርያም በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት በጨርጨር አውራጃ በሀብሮ ወረዳ መቻራ በምትባል አካባቢ ተወለዱ።
አባ ገብርኤል
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አባ ገብርኤል
አባ ገብርኤል።
አስፋው ተፈራ Asfaw Tefera
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
በ፲፱፳፫ ዓ.ም. በአሰበ ተፈሪ ደጋማው ክፍል ልዩ ስሙ ካራቆሬ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ፡፡ አቶ አስፋው ተፈራ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአሰበ ተፈሪ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በአዲስ አበባ ተግባረዕድ ት/ቤት ቴክኒክና ሙያ፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ መምህራን ማሠልጠኛ በመግባት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ በለንደን ስኩል ኦፍ ኦሪየንታል ኤንድ አፍሪካ ጉዳዮች ጥናት በዲግሪ፣ በሕዝብ አስተዳደር ደግሞ በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡
ከአሥራ ሁለት በላይ የታተሙ ሥራዎች አሏቸው፡፡ ከኀትመት ውጤታቸው መካከል የቤተክርስቲያን ታሪክ ለሕጻናት መማሪያ፣ ጠቅላላ የጂኦግራፊ መጽሐፍ፣ የአፍሪካ ጂኦግራፊ አጭር የዓለም ታሪክ፣ መክሰተ ሰዋሰው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት የቼምበር ማተሚያ ቤት፣ የኢምፔሪያል ሆቴልና የኢምፔሪያል አግሮ ኢንዱስትሪ ባለቤት ናቸው፡፡
በአማርኛ ካሳተሟቸው መጻሕፍት ሌላ በእንግሊዝኛ ቋንቋ “አፍሪካ ፓስት ፕሬዘንት ኤንድ ፊውቸር”፣ “ዌስት አፍሪካን ፖለቲክስ”፣ “አፍሪካ ማርች ቱ ዩኒት” በሚሉ ርዕሶች መጻሕፍት ጽፈው አሳትመዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
በ፲፱፳፫ ዓ.ም. በአሰበ ተፈሪ ደጋማው ክፍል ልዩ ስሙ ካራቆሬ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ፡፡ አቶ አስፋው ተፈራ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአሰበ ተፈሪ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በአዲስ አበባ ተግባረዕድ ት/ቤት ቴክኒክና ሙያ፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ መምህራን ማሠልጠኛ በመግባት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።
[1860 - 1939]
ፕሮፌሰር አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ Afework Gebreyesus
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ በ1860 ዓ.ም ጎንደር ዘጌ በተሰኘችው ስፍራ ተወለዱ፡፡ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል የሥጋ ዝምድና እንዳላቸው የሚነገርላቸው አፈወርቅ በልጅነት ዕድሜያቸው አዲስ አበባ መጥተው አደጉ።
ለዘመናዊት ኢትዮዽያ ሥልጣኔ መስራች የሆኑት ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ ያውሮፓን ሥልጣኔ ቀስመው እንዲመጡ ወደውጭ ሀገር ከላኳቸው ብልህ ወጣቶች መካከል አንዱ አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ ናቸው።
አፈወርቅ የ20 ዓመት ብላቴና ሳሉ በአጤ ምኒልክ በጎ ፈቃድ ከሁለት ወጣቶች ልጅ ጉግሳ ዳርጌ እና ልጅ ቅጣው ዛማኑኤል ጋር በ1880 ዓ.ም ወደ ስዊዘርላንድ ተላኩ። ከዚያ ከደረሱ በኋላ በገዛ ፈቃዳቸውና ባልታወቀ ምክንያት ወደ ጣሊያን ቱሪን ሄደው በኮሌጅ ኢንተርናሲዮናል ደ.ቤሊ አርቲ ከፍተኛ የሥነ ጽሑፍ ትምህርት ተከታተሉ። ከአድዋ ጦርነት በ1986 በፊት ወደ ኢትዮዽያ ተመልሰው በ1882 በቤተመንግስት ባለሟልነትና በሠዓሊነት ሙያ ያገለገሉት አፈወርቅ፥ በተለይ ከእቴጌ ጣይቱ ጋር በመቀያየማቸው በ1888 ዓ.ም. በስደት መንፈስ ወደ ኢጣሊያ ተመለሱ። በናፖሊ የምስራቅ ጥናት ኢንስቲቲዩት የአማርኛ ቋንቋ በማስተማር የፕሮፌሰርነት ማእረግ አግኝተዋል።
አፈወርቅ በኢጣሊያ ሳሉ ለኢትዮዽያ ዘመናዊ ሥነ ጽሁፍ ዕድገት የበኩር ልጅ ሊያሰኙዋቸው የቻሉትን የአማርኛ መጻሕፍት የጻፉ ሲሆን እንደገና ወደሀገራቸው በ1922 ዓ.ም. እስከተመለሱ ድረስ፥ በግእዝ፥ በአማርኛ፥ በኢጣሊያንኛ እና በፈረንሳይኛ ቋንቋዎች የመማሪያ መጻሕፍት፥ የታሪክ እና የፈጠራ ልቦለድ መጻሕፍትን አሳትመዋል።
አፈወርቅ በ1902 ዓ.ም. ሮማ ባሳተሙት ዳግማዊ ምኒሊክ በሚለው የታሪክ መጽሐፋቸው ከግዕዝ ጽሑፍ ባህል ወደ ዘመናዊ አማርኛ ኪናዊ ሥነጽሑፍ ለተደረገው ሽግግር በተለይ በ1908 ዓ.ም. በሮም ባሳተሟት ጦቢያ-ልቦለድ ታሪክ የፈጠራ ሥራቸው-በኢትዮዽያ የአማርኛ ዘመናዊ ሥነጽሑፍ መሥራች ካሰኛቸው ማእረግ ባሻገር በአፍሪካ ቋንቋዎችም ታሪክ- በሀገርኛ ቋንቋ በመጻፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ የሚል ምስክርነት አግኝተዋል።
ቀደም ሲል ለሀገራቸው በአስተርጓሚነት፥ በጉምሩክ ሥራ ኃላፊነት ነጋድራስነት እና በአምባሳደርነት ሮም ያገለገሉት አፈወርቅ በኢትዮዽያና ኢጣሊያን ጦርነት ወቅት 1924 - 1933 ኢጣሊያን ወገን ሆነው በ የቄሣር መንግስት መልእክተኛነት በሀገራቸው ልዩ በደል ፈጽመዋል በሚል ከነፃነት በኋላ በ1933 የዕድሜ ልክ እሥራት ተፈርዶባቸው በጅማ ጅሬን እሥር ቤት ለ6 ዓመታት በግዞት ቆይተው፥ በእርጅና እና በጤና ማጣት መስከረም 15 ቀን 1939 ዓ.ም በ79 ዓመታቸው አረፉ።
ምንጭ:
ብርሀነመስቀል ደጀኔ 2000ዓ.ም ብራና.ማ.ቤ ካሌንደር።
አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ በ1860 ዓ.ም ጎንደር ዘጌ በተሰኘችው ስፍራ ተወለዱ፡፡ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል የሥጋ ዝምድና እንዳላቸው የሚነገርላቸው አፈወርቅ በልጅነት ዕድሜያቸው አዲስ አበባ መጥተው አደጉ።
[1919 - 1976]
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ ገብረማርያም Afeworkyohanese Gebremariam
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
በአዲስ አበባ ከተማ በ፲፱፲፱ ዓ.ም. የተወለዱት ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ የቄስ ትምህርትን ከማይጨው ዘመቻ በፊት አጠናቅቀዋል፡፡ በጣሊያን የወረራ ወቅት በኢጣልያን ትምህርት ቤት ገብተው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል። በ፲፱፴፭ ዓ.ም. በጦር ሠራዊት ውስጥ ወታደርነት በመግባት ወታደራዊ ትምህርት ተምረዋል፡፡
ከዚያም በ፲፱፴፯ ዓ.ም. ሐምሌ 10 ቀን በክብር ዘበኛ መድፈኛ ክፍል የከፍተኛ ቴክኒክ ት/ቤት ገብተው የአምስት ዓመታት ኮርስ ተከታትለዋል፡፡ በመድፈኛ መኮንንነት ደረጃ ተመርቀዋል፡፡ እስከ ሻምበልነት ማዕረግ ደርሰው የነበሩት ሻምበል አፈወርቅ በ፲፱፶፫ ዓ.ም. የመንግሥት ግልበጣ ሙከራ ተካፋይ ሆነዋል በመባል ለሦስት ዓመታት በእስራትና በግዞት ቆይተዋል፡፡ ከ፲፱፶፮ ዓ.ም. ጀምሮ በሬዲዮ ጋዜጠኝነት አገልግለዋል፡፡
ሻምበል አፈወርቅ በ፲፱፶፯ ዓ.ም. ግጥሞች፣ ለዘፈን ለትካዜ፣ ለደስታ እና ልዩ ልዩ ታሪኮች በሚል የሥነ ግጥም መጽሐፍ፤ በ፲፱፶፯ ዓ.ም. ችግረኞች በሚል ርዕስ ከዓለም ታላላቅ ድርሰቶች ተጠቃሽ የሆነውን ልብወለድ መጽሐፍ ተርጉመው አሳትመዋል፡፡ የኔ ግጥሞች፣ የዓለም አስደናቂ ልዩ ልዩ ታሪኮች፣ ፍቅር በሰዎች ዘንድ፣ የሞራል ግዴታ ስሜታዊ ግጥሞችንም አሳትመው አልፈዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
በአዲስ አበባ ከተማ በ፲፱፲፱ ዓ.ም. የተወለዱት ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ የቄስ ትምህርትን ከማይጨው ዘመቻ በፊት አጠናቅቀዋል፡፡ በጣሊያን የወረራ ወቅት በኢጣልያን ትምህርት ቤት ገብተው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
አባ ባሕርይ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አዛዥ ዘወልድ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አዛዥ ሲኖዳ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አፈወርቅ አዳፍሬ Afework Adafre
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አባ ጋስፓሪኒ ገብረማርያም
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አሸብር ገብረሕይወት Ashebir Gebrehiwot
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አስረስ የኔሰው Asrese Yeneneh
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አባተ መኵርያ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አለምፀሓይ ወዳጆ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ተባባሪ ፕሮፌሰር አቦነህ አሻግሬ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አቦነህ አሻግሬ ተባባሪ ፕሮፌሰር በቀድሞው ኢሉባቡር ክ/ሀገር ጎሬ ከተማ መጋቢት ፭ ቀን ፲፱፵፫ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ከ፲፱፶-፲፱፩ ዓ.ም. ድረስ ጎሬ ኢሊባቡር፣ ጋምቤላና አዲስ አበባ 10 2፣ ኮተቤ መምህራን ማሠልጠኛ ት/ቤት ገብተው በመምህርነት ሙያ ትምርታቸውን አጠናቀዋል። ከአ.አ. ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ጥበባት ክፍል በቴአትር ጥበብ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ሲሆን፣ ከአሜሪካ ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከቴአትር ጥበባት ክፍል የማስተርስ ዲግሪያቸውን ወስደዋል፡፡
አቦነህ አሻግሬ “ቅኝት”፣ “ባሕር ማዶ”፣ የተሰኙ ቴአትሮቻቸውን በብሔራዊ ቴአትርና በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት አሳይተዋል፡፡ “ኩኩ መለኮቴ”፣ “አባ ጉጉ”፣ “የሰማዩ ሰረገላ”፣ በመባል የሚታወቁ የሕጻናት ቴአትሮቻቸው፣ በአዲስ አበባ የሕጻናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት፣ ሜጋ አምፊ ቴአትር ለሕዝብ ታይተዋል፡፡ ለአዋቂዎች ያዘጋጇቸው “ሊቀማዕምር” “ኩረባ”፣ የተባሉ ተውኔቶቻቸውም እንዲሁ ለመድረክ በቅተዋል፡፡ “እንቁጢ እንቁጣጣሽና ሌሎች ልቦለዶች”፣ በሚል መጽሐፍ አሳትመዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አቦነህ አሻግሬ ተባባሪ ፕሮፌሰር በቀድሞው ኢሉባቡር ክ/ሀገር ጎሬ ከተማ መጋቢት ፭ ቀን ፲፱፵፫ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ከ፲፱፶-፲፱፩ ዓ.ም. ድረስ ጎሬ ኢሊባቡር፣ ጋምቤላና አዲስ አበባ 10 2፣ ኮተቤ መምህራን ማሠልጠኛ ት/ቤት ገብተው በመምህርነት ሙያ ትምርታቸውን አጠናቀዋል።
አባ ጎርጎርዮስ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አስታጥቃቸው ይሁን
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አምሳሉ አክሊሉ Amsalu Aklilu
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አውግቸው ተረፈ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1920 - 1996]
ኑርልኝ አበራ ጀምበሬ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አበራ ጀምበሬ በቀድሞ ሸዋ ክፍለ ሀገር ነሐሴ ፳፯/፲፱፳ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞው ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ገብተው አጠናቅቀዋል። ከዚያም በማስከተል በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ገብተው የቤ.ኤ እና የኤል.ኤል.ቢ BA LLB ዲግሪዎቻቸውን ወስደዋል፡፡ አበራ ጀምበሬ “ስለጋብቻችሁ”፣ “የቀ.ኃ.ሥ. በጎ አድራጎት ድርጅት መመሥረት”፣ “አባ ኮስትር”፣ “ብቸኛው ሰው”፣ “አባ ገስጥ”፣ “የእሥር ቤቱ አበሳ” በሚሉ ርዕሶች መጻሕፍት አሳትመው ለአንባቢያን ያበረከቱ ሲሆን ገና ያልታተሙ ሥራዎችም አሏቸው፡፡
አበራ ጀምበሬ በቀድሞ ሸዋ ክፍለ ሀገር ነሐሴ ፳፯/፲፱፳ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞው ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ገብተው አጠናቅቀዋል።
አሳምነው ቢረጋ Asamnew Birega
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አንዳርጋቸው አሰግድ Andargachew Asegid
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አማኑኤል አብርሃም
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አርአያ ሙሉጌታ Araya Mulugeta
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አበጀ አያልነህ ሙላት
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አያልነህ ሙላቱ በቀድሞው አጠራር በጎጃም ጠቅላይ ግዛት ኀዳር ፩፪ ቀን ፲፱፵፩ ዓ.ም. ተወለዱ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአገው ምድር፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደብረ ማርቆስ ትምህርት ቤቶች ተከታትለዋል። የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ አ.አ. ዩኒቨርሲቲና የወቅቱ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኀበር ባስገኘላቸው ነፃ የትምህርት ዕድል በመጠቀም በቀድሞዋ ቦቪየት ኀብረት፣ “በሞስኮ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ” በሥነ ጽሑፍና በጋዜጠኝነት በኤም.ኤ. ዲግሪ ተመርቀዋል፡፡
አያልነህ ሙላቱ “እሳት ሲነድ”፣ “የገጠሯ ፋና”፣ “የመንታ እናት”፣ “ዱባና ቅል”፣ “ጥበበኛዋ ጋለሞታ”፣ “ሰባራ ዘንግ”፣ “ዶ/ር ጋጋኖ” ወዘተ የተሰኙ ተውኔቶችን ለሕዝብ አቅርበዋል፡፡ አያልነህ ሙላቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም “ዓለም”፣ “ቅሪት”፣ “ቀዝቃዛው ትዳር” “ጧሪ ልጆች”፣ “ባል እና ሚስት”፣ “ግርዛት”፣ “መስከረም”፣ “ቡሄ”፣ “የእናት ጡት”፣ “ያለ ዕድሜ ጋብቻ”፣ የተሰኙ ድራማዎች ታይተውላቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሬዲዮም “ቤተሰብ”፣ “ሴት ተማሪ”፣ “ጠለፋ”፣ “ዶ/ር ሙሉ፣ “ሴት ለጓዳ”፣ “ሕግና ሕጋዊነት” ወዘተ . . . . የተሰኙ ተውኔቶችን ለሕዝብ አቅርበዋል፡፡
አያልነህ ሙላቱ፤ “የሥነ ጽሑፍ ቅኝት”፣ “የአሌክሳንደር ፑሽኪን አጭር የሕይወት ታሪክ”፣ “ማን ይሆን የበላ?”፣ “ጥገት ላም”፣ የተሰኙ መጻሕፍትንም ለኀትመት አብቅተዋል፡፡ “ጽጌረዳ ብዕር”፣ እና “ትግላችን”፣ በተሰኙ የሥነ ግጥም መድብሎች ውስጥም፣ ከሌሎች ደራስያን ጋር በመሆን ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻቸውም ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ለማግኘት በቅተዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አያልነህ ሙላቱ በቀድሞው አጠራር በጎጃም ጠቅላይ ግዛት ኀዳር ፩፪ ቀን ፲፱፵፩ ዓ.ም. ተወለዱ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአገው ምድር፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በደብረ ማርቆስ ትምህርት ቤቶች ተከታትለዋል።
ተሰማ አጥናፍሰገድ ይልማ Atinafe Yilama
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አጥናፍሰገድ ይልማ በቀድሞው አርሲ ክ/ሀገር ልዩ ስሙ “ጥቾ” በተባለ ቦታ ግንቦት ፳፯ ቀን ፲፱፳፱ ዓ.ም. ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞ ቀ.ኃ.ሥ. ጢቾ ትምህርት ቤት በ፲፱፵፰ ዓ.ም. አጠናቀቁ፡፡ ከዚያም በ፲፱፶፩ ዓ.ም. አዲስ አበባ ንግድ ሥራ ት/ቤት ገብተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ፈጸሙ፡፡ በፖለቲካል ሳይንስና ሥነ መንግሥት ተጨማሪ ዕውቀት ገብይተዋል፡፡ አጥናፍሰገድ ይልማ “የበደል ካሳ” በሚል ርዕስ ታሪካዊ ልቦለድ መጽሐፍ አሳትመው ለአንባቢያን አቅርበዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አጥናፍሰገድ ይልማ በቀድሞው አርሲ ክ/ሀገር ልዩ ስሙ “ጥቾ” በተባለ ቦታ ግንቦት ፳፯ ቀን ፲፱፳፱ ዓ.ም. ተወለዱ።
አያሌው ሲሳይ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አቢይ አበበ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1943 - 2009]
መሪራስ አማን በላይ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
መሪራስ አማን የተወለዱት መጋቢት ፳፫ ቀን ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. አፕሪል 1 ቀን 1951 ዓመተ ምህረት) ሲሆን፣ የትውልዳቸው ስፍራቸው በለሳ ተብሎ በሚጠራና ጎንደር ውስጥ በሚገኘ አካባቢ ነበር። የአደጉትም በጎንደር እና በጎጃም ውስጥ ነበር ከልጅነታቸው ጀምሮ ትምህርታቸውን የቀሰሙት ከአባታቸው ከመምህር በላይ ድሉ፣ ከአባ ጼሄማ በጎንደር ተክለኃይማኖት፣ ከመሪጌታ መንክር ደብረኤልያስ ጎጃም፣ ከመሪጌታ ጉባኤ በጎጃም ነበር።
መሪራስ አማን፤ ቅዳሴን፣ ቅኔን፣ ዜማን፣ ብሉይን፣ ሃዲስን፣ የእንጨት አዋጅን (የመድኃኒት እጽዋትን)፣ የሃረግ ስዕልን፣ የኢትዮጵን ታሪክ፣ አቡሻህርን (ባህረሃሳብን) እና ሌሎችንም በአድባራት እና ገዳማት የሚሰጡ የኢትዮጵያ ትምህርቶችን ተምረዋል። በለተይ በቅኔ፣ በግስ ርባታ እና ሰዋሰው ችሎታቸው በመምህራኖቻቸው እና የትምሀርት ባልንጀሮቻቸው ስማቸው የተጠራ ነበር። በዚህም ምክንያት በጎጃም በይስማ ደጀን በመሪጌታ መንክር ዘንድ ቅኔ አስነጋሪ ነበሩ።
ተማሪ ሳሉ እና ትምህርታቸውንም ካጠናቀቁ በኋላ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተዘዋወሩ አያሌ ገዳማትን እና አድባራትን እየጎበኙ በውስጣቸው የአሉትን ምስጢራዊና ጥንታዊ መጻሕፍቶቻችንን ለመመርመር እድል አግኝተዋል።
የ19 ዓመት ልጅ ኹነው ወደ ኑብያ (ሱዳን) ተጉዘው በነበረበት ወቅት በአንድ በፈራረሰ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቤተክተርስቲያን ቅጥር ግቢ በተቀበረ የድንጋይ ሳጥን ውስጥ፣ ምናልባት ኢትዮጵያ ውስጥ የሌሉ የኢትዮጵያን ታሪክ ጨምሮ ስለተለያዩ ጉዳዮች የሚዘረዝሩ በግዕዝ የተጻፉ የብራና መጻሕፍትና ጥቅሎች አግኝተዋል። እነዚህን መጻሕፍት ያገኙት የዛሬ 50 ዓመት አካባቢ ነበር። መጻሕፈቱ በግዕዝ የተደረሱ ነበሩ። በእነዚህ መጻሕፍት ላይ ተመርኩዘው ይዘታቸውን እያሳጠሩ ከ24 ያላነሱ መጻሕፍትን አሳትመው፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸውን በእውቀትና በጥበብ አንጸዋል።
መሪራስ አማን በላይ መጽሐፍ ከማንበብና ከመጻፍ በላይ ሌላ ሕይወት አልነበራቸውም። በራሳቸው የተመዘገቡት የመጻሕፍቱም ዝርዝር የሚከተሉት ናቸው።
1. ምዕራፈ ሕያዋን ቃለ ሕይወት ዘወንጌላውያን የምሳሌው ምስጢር በሐተታና በትንተና
2. የጥንትዋ ኢትዮጵያ ትንሳዔ ታሪክ
3. የሱባ ቋንቋ መዝገበ-ቃላት
4. መጽሐፈ ብሩክ (ብሩክ ዣንሽዋ)
5. መጽሐፈ ክቡር
6. መጽሐፈ ሱባኤ ዘበአማን ካልእ
7. መጽሐፈ አብርሂት
8. መክሰተ ምስጢር
9. መጽሐፈ እንቆአእባን
10. መጽሐፈ ሠረገላ ታቦር
11. መርሐ ጽድቅ ወአሚን ወመርሐ ግብር
12. መጽሐፈ ፈውስ
13. መጽሐፈ አድህኖት
14. ብርሃነ ሕይወት ዘበአማን
15. መጽሀሠይፈ ኃይማኖት ተዋህዶ
16. ሕይወት እንደገና በሦስት ዐለሞች
17. በአንድ ሰውነት የሦስት አካላት ምስጢር
18. መጽሐፈ ኤልያስ ነቢየ እግዚአብሔር
19. የእውነትን ሕይወት ውደዱ
20. አፍሪ-ካሁን
21. ጥበብ ከእውቀት ትምህርት ከልጅነት
22. የልቤ ወዳጅ የሰው ዘር ልጅ
23. ጸሎት አሚን ዘበአማን ወጸሎተ ተዋህዶ
24. ምክር ከእኔ ስማ አንተ ወገኔ
መሪራስ አማን በላይ፣ በሀገር ፍቅር የሚነዱ፣ ለኢትዮጵያ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን ቀናኢ፣ ለኢትዮጵያ እውነተኛ ታሪክ መገለጥና መዛመት የሚተጉ እና በፍቅረ ንዋይ ያልተነደፉ ትልቅ ጠቢብ ነበሩ። ጥበብን ለአገራቸው ሕዝብ ለማቅሰም ወደኋላ አይሉም ነበር። ለአገራቸው እስከዛሬ ካበረከቱት በላይ ገና ብዙ አስተዋጽኦ ለማድረግ ቢያቅዱም የማይቀረው ሞት ቀደማቸው። ይህም በመሆኑ፣ ራሱ የእውቀት ዩኒቨርሲቲ የሆነ አንድ ትልቅ ሰው ኢትዮጵያ አጥታለች።
የተከበሩት ባለታሪክ፣ ፈላስፋ፣ ባለመድኃኒት፣ የነገረ-መለኮት አዋቂ እና የ24 መጻሕፍት ደራሲ የነበሩት መሪራስ አማን በላይ ባደረባቸው ሕመም የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. ፌብሩዋሪ 17 ቀን 2017) በሎስ አንጀለስ ከተማ በተወለዱ በ65 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ምንጭ ኢትዮጵያ ዛሬ ድረገጽ
መሪራስ አማን የተወለዱት መጋቢት ፳፫ ቀን ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. አፕሪል 1 ቀን 1951 ዓመተ ምህረት) ሲሆን፣ የትውልዳቸው ስፍራቸው በለሳ ተብሎ በሚጠራና ጎንደር ውስጥ በሚገኘ አካባቢ ነበር።
አማረ አፈለ ብሻው
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አድማሱ ጀምበሬ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አገኘሁ እንግዳ Agegnehu Engida
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አለማየሁ ሞገስ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዓለማየሁ ሞገስ በ፲፱፲፰ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ባህላዊ ትምህርት ቤት ገብተው ዜማ ተማሩ፡፡ ጣሊያን ሀገራችንን በወረረች ጊዜ የአርበኝነት ግጥም እየገጠሙ የአርበኞችን ወኔ ይቀሰቅሱ ነበር። የግዕዝን ዐዋጅ አገባብና የቅኔን ሥርዓት በአጭር ጊዜ የተማሩት በግላቸው ጥረት በቤት ውስጥ ነበር። ከዚያም በ፲፱፴፮ ዓ.ም. በቅኔ መምህርነት ተመረቁ፡፡ በ፲፱፴፰ ዓ.ም. ዘመናዊ ትምህርት ጀመሩ፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና በታሪክ ሁለት የቢ.ኤ.ዲግሪና በኢጣሊያን አገር የሥነ ጽሑፍ ዲግሪ አግኝተዋል። በተጨማሪም ግዕዝ፣ ትግርኛ፣ ግሪክ፣ ጣሊያንኛ፣ ፈረንሳይኛና እንግሊዝኛ ቋንቋ ያውቃሉ። ላቲን ዐረብኛና ቱርክ ያነባሉ። አብዛኞቹ መጻሕፍታቸው በግዕዝ ማስተማሪያነት የሚያገለግሉ ሲሆን በልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የጻፏቸውም ድርሰቶች ቁጥር በርካታ ናቸው።
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማህበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
ዓለማየሁ ሞገስ በ፲፱፲፰ ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ባህላዊ ትምህርት ቤት ገብተው ዜማ ተማሩ፡፡ ጣሊያን ሀገራችንን በወረረች ጊዜ የአርበኝነት ግጥም እየገጠሙ የአርበኞችን ወኔ ይቀሰቅሱ ነበር።
አስረስ አስፋወሰን Asrese Asfawosen
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አበራ ለማ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አበራ ለማ የተወለደው በ ፲፱፵፫ ዓ.ም. ፍቼ ሰላሌ ውስጥ ነው። እድገቱ ወሊሶንና አዲስ አበባን ያካትታል። ካገራችን ገጣሚያንና አጫጭር ልቦለድ ጸሓፊዎች አንዱ ነው። በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ ጥናት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የማዕርግ ተመራቂ ነው።
ሙያው ጋዜጠኘት ሲሆን፣ በማስታወቂያ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ሬዲዮና ፕሬስ መምሪያዎች ሠርቷል። ከጦር ግምባር ጋዜጠኝነት እስከ የሕዝብ ማመላለሻ ኮርፖሬሽን የማስታወቂያና ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት ኃላፊነት ዘልቋል። በተለያዩ የኪነጥበባት ዘርፎች ነቃሽ ሃያሲነትም ይታወቃል።
እስከ ሰማንያዎቹ አሠርት አጋማሽ ድረስ፥ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ዋና ጸሃፊ ሁኖ አገልግሏል። ዛሬ የኖርዌይ ነዋሪ ነው።
ኖርዌይ ደራስያን ማኅበር ብቸኛውና የመጀመሪያው ጥቁርና ባፍ መፍቻ ቋንቋው የሚጽፍ አባል ደራሲ ነው። በዚህ ማኅበር ውስጥ የዓለም አቀፍ ኮሚቴው የረዥም ዘመን አባል በመሆንም ይታወቃል።
ባለቅኔ ሎሬትጸጋዬ ገብረመድህንንና (2005 እ.ኤ.አ.) ስዊድናዊ/ኤርትራዊ የሆነውን የአሥመራውን እስረኛ ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅን (2009 እ.ኤ.አ.) ሃሳብን በነጻ የመግለጽ ሽልማት እንዲሸለሙ በማድረጉም በሰፊው ይታወቃል።
አበራ ለማ የተወለደው በ ፲፱፵፫ ዓ.ም. ፍቼ ሰላሌ ውስጥ ነው።
[1912 - 1961]
አሰፋ ገብረማርያም ተሰማ Asefa Gebremariam Tesema
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አቶ አሰፋ ገ/ማርያም ተሰማ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ፡፡ አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርበኞች ት/ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጄኔራል ውንጌት ት/ቤት ተምረዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በቀድሞው ሶቪየት ኀብረት ሌኒን ግራድ ዩኒቨርሲቲና በእንግሊዝ ሀገር በሚገኘው ኢንደንብራ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ሰልጥነዋል፡፡
ለኀትመት የበቁላቸው ሥራዎች "የመስከረም ጮራ"፤ እና “The Voice” የተሰኙ የግጥም መድብሎች ይጠቀሳሉ፡፡ በቲአትር ዘርፍ "ዩሊየስ ቄሳር"፣ "ዋናው ተቆጣጣሪ" የትርጉም ሥራዎች እና "ከለንደን አዲስ አበባ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ወጥ ቲአትር ለመድረክ አብቅተዋል፡፡ የደርግ ዘመንን ብሔራዊ የሕዝብ መዝሙርም ደርሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኀበርን በዋና ፀሐፊነት መርተዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አቶ አሰፋ ገ/ማርያም ተሰማ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ፡፡ አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርበኞች ት/ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጄኔራል ውንጌት ት/ቤት ተምረዋል።
አድማሱ ደስታ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አማኑኤል መሐሪ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አስፋው ዳምጤ Asfaw Damte
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አበበ አይቸህ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አንድአርጌመስፍን ሽፈራው Andargemesfine Shiferaw
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አንዳርጌ መስፍን ሚየዝየ ፰ ቀን ፲፱፵፫ ዓ.ም. ልዩ ስሙ “አባጭመና መስክ” በተሰኘ ቀበሌ ጎንደር ክ/ሃገር ተወለዱ። ከ፲፱፶፪ - ፲፱፶፬ ዓ.ም. በቤተክህነት ውስጥ የቀለም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ከ፲፱፶፭ - ፲፱፷፪ ዓ.ም. የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተወለዱበት ቀበሌ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እስከ ፲፱፷፮ ዓ.ም. ጎንደር ከተማ ውስጥ ተምረዋል፡፡ ከ፲፱፹፪ - ፲፱፹፬ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት የተከታተሉ ሲሆን በጦር ሠራዊት ውስጥ አገልግሎት እየሰጡ ስለአየር መቃወሚያና ሌሎች ወታደራዊ ዘዴዎች ተጨማሪ ዕውቀት አግኝተዋል፡፡
አንዳርጌ መስፍን “ዳር እስከዳር”፣ “ጥቁር ደም”፣ “ጥልፍልፍ”፣ “ቅሌት”፣ “ደም በደም” በሚሉ ርዕሶች የተጻፉ ልቦለድ ሥራዎች አሉዋቸው፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አንዳርጌ መስፍን ሚየዝየ ፰ ቀን ፲፱፵፫ ዓ.ም. ልዩ ስሙ “አባጭመና መስክ” በተሰኘ ቀበሌ ጎንደር ክ/ሃገር ተወለዱ።
አዳም ረታ ብዙነህ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አዳም ረታ ሐምሌ ፰ ቀን ፲፱፵፱ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በባልቻ አባነፍሶ ት/ቤት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በልዑል መኮንን ት/ቤት፣ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ ከአ.አ. ዩኒቨርሲቲ ተከታትለው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ይዘዋል። በጂኦግራፊ ሙያ ልዩ ዘርፍ ሠልጠጥነዋል፡፡ በ፲፱፸፯ ዓ.ም. በታተመው “አባ ደፋርና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች”፣ መድብል ውስጥ አራት አጫጭር ልቦለድ ድርሰቶችን አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም “ማኀሌት”፣ “ግራጫ ቃጭሎች”፣ የሚሉ መጻሕፍትን ለአንባብያን አቅርበዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
አዳም ረታ ሐምሌ ፰ ቀን ፲፱፵፱ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በባልቻ አባነፍሶ ት/ቤት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በልዑል መኮንን ት/ቤት፣ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ ከአ.አ. ዩኒቨርሲቲ ተከታትለው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ይዘዋል።
አሰፋ ጉያ Asefa Guya
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ኮ/ል አስራት ቦጋለ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1926 - 1979]
ኢዩኤል ዮሐንስ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ኢዩኤል ዮሐንስ ሰኔ ፳፩ ቀን ፲፱፳፯ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ። የቅኔ፣ የዜማና አቋቋም ትምህርትን በቤተ ክህነት፣ የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በማታው ክፍለ ጊዜ ከካቴድራል ትምህርት ቤት አጠናቀዋል፡፡
በለንደን ድራማ ማዕከል ሴንተር ልዩ የድራማ ኮርስ ተምረውና በሙያው ሠልጥነው በቴአትር ቤት አስተዳደር /ማኔጅመንት እና በመድረክ ዳንስ አቀናባሪነት ዲፕሎማና ሰርተፊኬት አግኝተዋል፡፡
ኢዩኤል ዮሐንስ ከ፲፱፴፭ ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ሕዝብ የሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ውስጥ ከ 65 ያላነሱ ረዣዥምና አጫጭር ድራማዎችን፣ ኢትዮጵያዊ ኦፔራ፣ ሙዚቃዊ ድራማ፣ ልዩ ልዩ ግጥሞችን፣ ሽብሸባዎችን፣ የብሔርና ብሔረሰብ ዳንኪራና ጭፈራዎችን፣ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ መድረክ ማቅረብ የቻሉና ልዩ ስጦታ የነበራቸው የጥበብ ሰው ነበሩ፡፡
ኢዩኤል ዮሐንስ ዘፈኖችንና መዝሙሮችን ከላይ በተጠቀሰው ቴአትር ቤት፣ በብሔራዊ ቴአትር በሲኒማ ራስ፣ በወ.ወ.ክማ፣ በዩኒቨርሲቲ፣ በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች፣ በክፍላተ ሀገራት በሚገኙ አውራጃዎችና ወረዳዎች፣ እንዲሁም በቴሌቪዥንና በሬዲዮ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከማቅረባቸውም ባሻገር በአፍሪካ፣ በአውሮፖ፣ በእስያና በሩቅ ምሥራቅ አህጉራት መድረኮች ላይ በመገኘትም የኢትዮጵያን ባህል በስፋት አስተዋውቀዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
ኢዩኤል ዮሐንስ ሰኔ ፳፩ ቀን ፲፱፳፯ ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ተወለዱ።
ኢብንፈድል አላህ ኣል ዑምሪ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ኤፍሬም እንዳለ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ኤልያስ ነብየልዑል
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1462 - 1552]
እጨጌ እንባቆም
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1924 - 1983]
ሊቁ ዶ/ር እጓለ ገብረ ዮሐንስ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዶ/ር እጓለ ገብረ ዮሐንስ የካቲት 6 ቀን 1924 ዓ/ም ከአባቱ ከመምሬ ገብረ ዮሐንስ ተሰማና ከእናቱ ከወ/ሮ አመለወርቅ ሀብተ ወልድ አዲስ አበባ ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ አጥቢያ ተወለደ:: ዕድሜዉ ለትምህርት ሲደርስ በዚሁ ደብር ፊደል ቆጥሮ ዳዊት ደግሟል:: ዳዊቱን: በቃሉ ጭምር ያውቀው ስለነበረ የዳዊት መጽሐፍ ባላገኘ ጊዜ በዓቢይ ጾም ዳዊት በሚተዛዘልበት ወቅት በቃሉ ያስተዛዝል ነበረ።
ቀጥሎም የዜማ ትምህርት ከመሪጌታ ኃይለ ጊዮርጊስ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ወንበር ዘርግተው ከሚያስተምሩት ዘንድ ገብቶ ጾመ ድጓን ዘልቆአል:: በዚያን ጊዜ ከእየደብሩ 2:2 ልጆች እየተመረጡ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት እንዲገቡ ጥሪ ስለደረሰ ከሁለቱ ተመራጮች አንዱ ሆኖ ቅድስት ሥላሴ ትምህርት ቤት ገብቶ በዘመናዊ ትምህርት ስምንተኛን ክፍል አጠናቅቆ ሁለተኛ ደረጃ እንዳለ ወደ ግሪክ አገር እንዲሄድ ስለተመረጠ በ1943 ዓ/ም ወደ ግሪክ አገር ሄዶ ቆሮንጦስ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቅቋል:: እዚያ በነበረ ጊዜ ዝንባሌው ግልጽ እየሆነ ሄደ:: ፍልስፍና ትምህርት ላይ ትኩረት ስለአደረገ የፍልስፍናን መጽሐፍት በብዛት እየገዛ ያነብ ነበር:: የህ የጋለ ፍቅር እስከ መጨረሻ ሕይወቱ አልከሰመም:: የመጽሐፍ ሱሰኛ ቀበኛ እንደነበር በዚህ አደባባይ ሳልገልጠው አላልፍም:: ብዙዎቹን መጽሐፍቱን ለተመለከታቸው በእርሳስ ተዥጐርጉረው ገጾቻቸው ተበሳስከው ነው የሚገኙት:: አመለኛ ጎብኝቶአችዋል ማለት ነው::
ወደ: ነገሬ ልመለስና የቆሮንጦስን ትምህርት ቤት ሲጨርስ ንግግር እንዲያደርግ የተወሰነው እርሱ ነበር:: ንግግሩ ቅደም ተከተሉ የሠመረ ብቻ ሳይሆን ለለጋ ዕድሜዉ ጥልቅ የፍልስፍና ሐሳብን ያዘለ ነበር:: በዚያን ጊዜ በወቅቱ የአቴን ዩኒቨርስቲ መንፈሳዊ መምህራን እንዲገኙ ተጋብዘው ነበር:: እጓለ ንግግሩን ሲጨርስ አንድ የዩኒቨርስቲ መምህር ከመቀመጫው ተነሥቶ ሒዶ ስሞ አመስግኖታል::
አቴን ዩኒቨርስቲ መንፈሳዊ ትምህርትን ከፍልስፍና ጋር አዛምዶ አእምሮውን ያንጽ ጀመር:: ለትምህርት የነበረው ፍቅር በአርእያነት የሚጠቀስ ነበር:: የተወሰነውን የአራት ዓመታት ትምህርት ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ጀርመን ሀገር ሄዶ ቦን ዩኒቨርስቲ ከፍልስፍና ፉከልቲ ተመዝግቦ ያ የሚጓጓለትን ፍልስፍና ይዋኝበት ጀመር:: በዘመኑ ከቦን ዩኒቨርስቲ በዓለም መድረክ የታወቁ መምህራን ያስተምሩ ነበር:: የእነርሱን ትምህርት ሳያስታጉል በጥንቃቄ ያዳምጥ ነበር:: በግልም እያነጋገረ ስለ ፍልስፍና ትምህርት አጠናንና አቀራረብ መመሪያ ይቀበል ነበር:: ይህም አልበቃ ብሎ በሌላ ዩኒቨርስቲ አንቱ የተባሉና በዓለም መድረክ ያንጸባረቁ ለምሳሌ ፍራይቡርግ ዩኒቨርስቲ Martin Heidegger ሀይደልበርግ ዩኒቨርስቲ Karl Jaspers ያስተምሩ ስለነበር እዚያ ያሉበት ድረስ እየሄደ ትምህርታቸውን አዳምጧል:: ሁለቱም እንደሚታወቀው Existentalist Philosophers ናቸው:: የ Martin Heidegger የታወቀው ሥራ “ጊዜና መሆን” Time and Being የሚለው ምን ያህሉንም እጓለን ያረካ አልመሰለኝም የ Jaspers ን “እውነት” Von der Wahrheit የሚለውን ግን ከአንደበቱ የማይለየው ነበር: ሁሉንም ባይሆንም እንኳ አብዛኛዎቹን የዚህን ፈላሰፋ ድርሰቶች ገዝቶ ከግል ቤተ መጻሕፍቱ አከማችቶአል:: ምናልባት ወደዚህ ፈላስፋ መንፈሱ ያጋደለው ሚዛናዊና ኅላፊነት የተሞላ አስተሳሰብ ስላለው ሳይሆን አልቀረም::
ቀደም ካሉት ፈላሰፋዎች የሚያደንቃቸው አፍላጦንን ፕሌቶንና ኢማኑኤል ካንትን ነበር:: የአፍላጦን “ሪፑብሊክ” የካንትን “የንጹሕ አእምሮ ሒስ” Critique of Pure Reason የሚባሉት አዘውትሮ ደጋግሞ የሚያነባቸው መጽሐፍት ነበሩ:: ምናልባት ከመጽሐፍ ቅድስ ለጥቆ በሁለተኛ ደረጃ የሚመደቡ ሳይሆኑ አልቀረም::
የእጓለ አስተሳሰብ የተመሠረተው በሶቅራጥስ ጥያቈና ምላሽ ዘዴ ላይ ነበረ:: ስለ: እውነት ሲባል የአንድን ሐሳብ ደካማና ጠንካራ ጐን እየገመገሙ እስከ መጨረሻዉ ሂደት ማድረስ ነበር:: በምንም ዓይነት በሚከራከርበት ወቅት አይቆጣም:: የሚቆጣ ሰው እንኳን ቢያጋጥመው አለሳልሶ ወደ ጤናማ ክርክር ይመልሰዋል:: በምዕራብ አስተሳሰብ ገጸ ባሕርይና ሐሳብ የተለያዩ ናቸው ምንም እንኳን አንዱ ከሌላው ጋር የተያያዘ ቢሆንም:: ሐሳቡን መንቀፍ ሰውየውን ማዋረድ አይደለም::
ከባለ ቅኔዎች ደግሞ አሊጌሪ ዳንቴን ፤ ፍሪድሪክ ዊልሔም: ጆሴፍ ቮን ሽለርንና ዮሐንቮልፍጋንግ ቮንጌቴን በተለይ ይወዳል:: እንደ ባለቅኔዎቹ ቅደም ተከተል በዚያኑ መጠን ፍቅሩ እያየለ ይሄዳል:: ጌቴ ላይ ሲደርስ ፍቅሩ ይጠናል:: ከፊተኞቹ ሁለቱ ላይ ቀንጨብ እያደረገ በስንኝ ወደ አማርኛ ተርጉሟል:: ከዳንቴ መካነ ንስሐ ከመግቢያው ተርጉሞ ከመጽሐፉ ውስጥ ጨምሮ አሳትሞታል:: እንዲሁም ከሽለር “ዋስትና” የሚለውን ተርጉሟል:: ይበልጥ ያተኮረው ግን ጌቴ ላይ ነበር:: “ፋውስትን በሙሉ በሰንኝ ለመተርጐም አቅዶ ጀምሮ አካሂዶታል:: ነገር ግን ዳር ሳያደርሰው በሞት ተቀደመ:: እንደዚሁ በጅምር የቀሩ “ከተረት ወደ ኅሊና” የሚል የፍልስፍና ድርሰትና “መዝሙረ ኢትዮጵያዊ” የሚል የግጥም ሰብስብ ይገኝበታል:: ቀደም ሲል የካንትን ሥነ ምግባር ለማስተማሪያ እንዲያገለግል ገና ከትምህርት ቤት እንዳለ ተርጉሞታል:: እጓለ የግጥም ተሰጥዎ በተጨማሪ ነበረው:: የግጥሙ ስልት የሚከተለው ከፍ ብለው በተጠሩት ባለቅኔዎች ፈር ነበር:: ሌላው ተዘጋጅቶ አልቆለት ሳይታተም የቀረ በአንቀጸ ብጹዓን ላይ የተመሰረተ የአባቱን ምግባረ ሠናይ የሚገልጽ በመንፈሳዊና በፍልስፍና ሐሳብ የተጠናከረ ሰፋ ያለ ጽሑፍ ነው:: የዚህን መጽሐፍ ታትሞ መውጣት ለማየት በጣሙን ይጓጓ ነበር::
ቦን ዩኒቨርስቲ የዶክተር ማዕረግ ካገኘ በኋላ ምኞቱ በከፍተኛ ተቅዋም ለማስተማር ስለነበረ የማስተማርን ዘዴ ለማጠናከርና የእንግሊዝኛ ዕውቀቱን ለማጎልበት እንግሊዝ አገር በርሚንግሃም ዩኒቨርስቲ ቆይቶ በ1953 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ:: ወዲያው ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተመድቦ ፍልስፍናን ማስተማር ጀመረ:: በዚያን ጊዜ ነው ፍልስፍና ለበስ ንግግሮችን በተከታታይ በራዲዮ ለሕዝብ ያሰማ የነበረው:: እነዚህንም ኋላ አሰባስቦ “የከፍተኛ ትምሀርት ዘይቤ” በሚል ርእስ አዲሰ አበባ በ 1956 ዓ/ም መጽሐፍ አሳትሟል:: በዚህም በኢትዮጵያ አስተሳሰብና በምዕራብ አስተሳሰብ መካከል ድልድይ ሠርቷል:: ስለዚህ በዚህ አገር በዘመናዊ ዐዋቂዎች ታሪክ ግንባር ቀደም እንዲሆን አስችሎታል :: ከዚሁ ጋር መጥቀስ የሚገባው በአስተማሪነቱ ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ራዲዮ የታወቀውን መምህር አብራራው በመባል የሚታወቀውን ፕሮግራም ስያሜውንም የሰጠ ፕሮግራሙንም የጀመረ ዶ/ር እጓለ መሆኑን ነው::
በ1956 ዓ/ም ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተዛዉሮ በቦን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አንደኛ ጸሐፊ ሆኖ ሠርቷል:: እዚያም 6 ዓመታት ያህል ካገለገለ በኋላ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት ተዛውሮ በአማካሪነት ማዕረግ የክፍል ኃላፊ በመሆን አገልግሏል:: በ 1965 ዓ/ም የመምሪያ ኃላፊ ሆኗል:: ከኅዳር ወር እስከ ስኔ ወር 1970 ዓ/ም በበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አማካሪ ሆኖ ሠርቷል:: ከጥር 1 ቀን 1972 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ጡረታ ክልል ገብቷል:: ከዚያን ጊዜ እስከ ዕለተ ሞቱ ባለው ዕድሜ ከፈጸማቸዉ ሥራዎች በኢትዮጵያ የመጽሐፍ ቅዱሰ ማኅበር አማካይነት የግዕዙን ሐዲስ ኪዳን ለማሻሻል በተቋቋመው ቡድን ያደረገው አስተዋፅኦ ጎላ ብሎ የሚታየ ነው:: ሐዲስ ኪዳንን በተለይ ጳዉሎስን በእናቱ በግሪኩ ዘር በቃሉ ጭምር የሚያውቀው በመሆኑ የእርሱ ድርሻ የላቀ እንደነበር ይገመታል::
1983 ዓ/ም እንደሚባለው ለእጓለ ጎደሎ ዓመት ነው:: ይህ ዓመት ከገባ አንሥቶ ፈጽሞ ጤና አልነበረውም:: ዓመቱ ሲጋመስ እንዲሁ ጤንነቱ ተጋመሰ:: እዚሁ አዲስ አበባ ሐኪም ቤት ገባ ፤ ግን ሕመሙ አልተሻለውም:: ለተሻለ ሕክምና ናይሮቢ ኬንያ ተላከ:: ሕክምናው አሁንም ውጤት አላሳየም:: መጋቢት 23 ቀን 1983 ዓ/ም ናይሮቢ ኬንያ ዐረፈ:: አስከሬኑ በአይሮፕላን ወደ አዲስ አበባ ተጓጉዞ መጋቢት 26 ቀን 1983 ዓ/ም ሥርዓተ ቀብሩ በቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን ተፈጸመ:: ወሩ ይለያይ እንጂ ወር በገባ በ23 አባቱ ያረፉበቱ ዕለት ነው:: አባት ልጃቸውን ጠሩ ልጅም ለአባቱ ታዘዘ::
ዶ/ር እጓለ ሚያዝያ 8 ቀን 1964 ዓ/ም ከወይዘሮ እሀትአፈራሁ ተስፋዬ ጋር በቁርባን ታጋብቶ 3 ልጆችን አፍርቷል::
ቸሩ አምላክ ነፍሱን ከአብርሃም ፣ይስሐቅና ያዕቆብ እቅፍ ያኑርልን::
የቅርብ ጓደኛቸው ዶ/ር ሥርግው ሐብለ ሥላሴ እንደጻፉት
http://www.facebook.com/Dr.Eguale/info
ዶ/ር እጓለ ገብረ ዮሐንስ የካቲት 6 ቀን 1924 ዓ/ም ከአባቱ ከመምሬ ገብረ ዮሐንስ ተሰማና ከእናቱ ከወ/ሮ አመለወርቅ ሀብተ ወልድ አዲስ አበባ ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ አጥቢያ ተወለደ:: ዕድሜዉ ለትምህርት ሲደርስ በዚሁ ደብር ፊደል ቆጥሮ ዳዊት ደግሟል:: ዳዊቱን: በቃሉ ጭምር ያውቀው ስለነበረ የዳዊት መጽሐፍ ባላገኘ ጊዜ በዓቢይ ጾም ዳዊት በሚተዛዘልበት ወቅት በቃሉ ያስተዛዝል ነበረ።
እንዳለ ጌታ ከበደ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1885 - 1972]
ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት በጉርሱም አውራጃ ኀዳር 1885 ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በወራት ጊዜ ውስጥ እናታቸው ሞቱ፡፡ ዕድሜያቸው አራት ዓመት ሲሆናቸው ወላጆቻቸው ከሞቱባቸው ሌሎች ልጆች ከሚያድጉበት ከራስ መኮንን ቤት እየተማሩ እንዲያድጉ ተላኩ፡፡ እዚያም በአብዛኛው ግዕዝና ሌሎች ትምህርቶች ተማሩ።
እምሩ ኃይለሥላሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በጣም ይታወቃሉ፡፡ ከምኒልክ ጊዜ ጀምሮ እስከ ደርግ ሥርዓት ድረስ መኖራቸው ደግሞ በበለጠ ለመታወቅ አስችሏቸዋል፡፡ ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ ከሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻቸው ስለኢትዮጵያ ፖለቲካ፣ ዲፕሎማሲና ወታደራዊ ታሪክ አጉልተው ጽፈዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት በጉርሱም አውራጃ ኀዳር 1885 ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በወራት ጊዜ ውስጥ እናታቸው ሞቱ፡፡ ዕድሜያቸው አራት ዓመት ሲሆናቸው ወላጆቻቸው ከሞቱባቸው ሌሎች ልጆች ከሚያድጉበት ከራስ መኮንን ቤት እየተማሩ እንዲያድጉ ተላኩ፡፡ እዚያም በአብዛኛው ግዕዝና ሌሎች ትምህርቶች ተማሩ።
ዶ/ር እግረጸሐይ ፍቅሬ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ኦላና ዞጊ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዑቍባሚካኤል ሀብተማርያም
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዓረፈዐይኔ ሐጎስ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዓለማየሁ ነሪ ውርጋሶ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዓለማየሁ ነሪ ቀኛዝማች እኖር ማፌድ በተባለ ሥፍራ ሐምሌ ፭ ቀን ፲፱፻፳፮ ዓ.ም. ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአልያንስ ፍራንሴዝና ሱዳን ኢንተሪየር ሚሽን ት/ቤቶች ከተማሩ በኋላ በሽመልስ ሀብቴ ትምህርት ቤት ገብተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቅቀዋል፡፡
ዓለማየሁ ነሪ “ኧሰት” የባህልና የታሪክ መሠረት አንደኛ መጽሐፍ፣ የባለታሪኮች ዳግም ልደት “ኧሰት” ሁለተኛ መጽሐፍ፣ ኢትዮጵያዊ ሲሳይ “ኧሰት” ሦስተኛ መጽሐፍ፣ በተከታታይ አሳትመው ለአንባብያን አቅርበዋል፡፡
ምንጭ:
የኢትዮዽያ ደራሲያን ማሀበር ለሚሊኒየም ያሳተመው አጀንዳ።
ዓለማየሁ ነሪ ቀኛዝማች እኖር ማፌድ በተባለ ሥፍራ ሐምሌ ፭ ቀን ፲፱፻፳፮ ዓ.ም. ተወለዱ።
ዐቃቤ ሰአት ከብቴ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
አባ ዐምደ ሐዋርያት
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዐሥራተማርያም
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዐሥራት ገብረማርያም
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዐረብ ፋቂው
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዐጽመ ጊዮርጊስ ገብረመሲሕ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
ዐምደጽዮን ተሰማ
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
[1306 - 1336]
ዐፄ ዐምደጽዮን
የደራሲውን ሥራዎች ዝርዝር ለማየት እዚህ ይጫኑ።
መጻሕፍት ለመዋዋስ መመዝግብ ያስፈልጎታል። ለመመዝገብ እዚህ
ይጫኑ
ተመዝግበው ከሆነ እዚህ
ይጫኑ
[
ታሪክ
|
ምርምርና ጥናት
|
ልቦለድ
|
ግጥምና ቅኔ
|
ተውኔት
|
ትምህርት
|
ፍልስፍና
|
ተረቶችና ቀልዶች
|
ትርጉም
|
ቋንቋ
|
ወግ
|
መንፈሳዊ ድርሰቶች
|
መዛግብተ-ቃላት
]
[
ዋና ገጽ
|
ስለኛ
|
አስተያየት
|
አድራሻችን
]
መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው© 2007 ዓ.ም ethioreaders.com